Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية  Portuguese
Top banner
Book of the day

ነቢል.pdf


  • word cloud

ነቢል.pdf
  • Extraction Summary

ይህ አስፀያፊ ነው። እርሱ ሞቶ ከነበረ ዓለምን ይገዛ የነበረው ማን ነበር። ወደ ገሃነም አንድሄድ ስለሚፈልጉ ነው ወይንስ የሚናገሩትን ነገር ስለማያምኑ ነው። በአሁኑ አውድ መልስ እንዴት መስጠት እንዳለብኝ ማሰብ ጀመርኩኝ አሁንም ድረስ አንደበቱ መቆለፉንና እኔም ከፍሉን ለቅቄ ለመውጣት መጣደፌን ካየች በኋላ የነገርኳትን ማመኗን እጠራጠራለሁ ሰበብ ፈጥሬ በጥድፍያ ወደ ላይኛው ደረጃ ወጣሁ ሁለተኛው ደረጃ ላይ የሚገኘውንም እንደሚጠቅስ ብሉምበርግ መናገሩ ትዝ አለኝ ምናልባት እርሱ ነገሮችን ግልፅ ያደርግልኝ ሆን መዝሙር ዝዐን በማውጣት የመጀመርያውን ቁጥር አነበብኩኝ ጌታ ጌታዬን ጠላቶችህን የአግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀፔ ተቀመጥ አለው ይላል ነገር ግን ከተሰማኝ ሰለም የተነሳ አንቅልፍ ወዲያውኑ ይዞኝ ነጎደ ለብዙ ጊዜ እግዚአብሔርን ከጄዋለሁ ኦገስት ከሌሊቱ ሰዓት ላይ በአልጋዬ ግርጌ ላይ በግንባሬ ተደፍቼ ጸለይኩኝ ራሴን ሰጥቻለሁ ኢየሱስ ከርስቶስ የሰማይና የምድር ጌታ መሆኑን በመቀበል እገዛለታለሁ ኃጢአቴን ለማንፃት ሲል ወደዚህ ምድር መምጣቱንና ጌትነቱን ከሙታን በመነሳት ማረጋገጡን እቀበላለሁ እኔ ኃጢአተኛ ነኝ ስለዚህ ከኃጢአቴ ለመንፃት እርሱ ያስፈልገኛል ጌታዬ ከርስቶስ ሆይ በሕይወቴ ውስጥ እቀበልሃለሁ። ለምን እዚህ ምድር ላይ ተውከኝ። ይህ አይገባቸውም ነበር። አያውቅም ልንነግረው ይገባል እኔ በግል ጉዳዮቼ ተወጥሬ ስባዝን በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ እግዚአብሔር ማን መሆኑን የማያውቁ አስደናቂ ፍቅሩን ያልቀመሱ ያደረገልንን ድንቅ ሥራ ያልተገነዘቡ ሰዎች በዓለም ዙርያ ይገኛሉ በትከከል በሥቃይ ውስጥ እያለፉ የሚገኙት እነርሱ ናቸው እርሱ የሰጠንን ተስፋ ሰላምና ከመታወቅ የሚያልፈውን ፍቅሩን አያውቁትም የወንጌሉን መልዕከት አያውቁትም ኢየሱስ ለእኛ ያለውን ፍቅር እጅግ የተዋረደ ሕይወት በመኖርና እጅግ አሣቃቂ አሟሟት በመሞት ካሳየ በኋላ እኔ እንደወደድኳቸሁ እርስ በርሳቸሁ ተዋደዱ በማለት አዞናል እርሱ እንደኖረው ለመኖር እርሱ እንደሞተው ለመሞት መወደድ የማይገባቸውን እንደወደደው ለመውደድና ተስፋ ለሌላቸው ተስፋን እአንደሰጠው ለመስጠት የማልፈልግ ከሆነ የኢየሱስ ተከታይ መሆኔን መናገር የምችለው አንዴት ነው።

  • Cosine Similarity

ሻ ተተኪዎች አንደሆኑ ከሚያምኗቸው አራት ኸሊፋዎች ሾሴቶ ዋና መሪ በሙስሊሞች ላይ ያለው መካከል አንዱ ነበርየዘር ግንዳችን በእርግጥም ከፍ ያለ ሥልጣን ብዙ የተከበረ ነው ቤተሰቦቼ በውርሶቻቸው ጊዜ ይህ መጠርያ የመሐመድን አራቱን መኩራታቸው አያስገርምም ተተኪዎች ለማመልከት ያገለግላል አባቴ በዎቹ ውስጥ ፓኪስታንን ለቆ እንዲወጣ ያስገደደው ለቤተሰቡና ለውርሶቹ የነበረው ፍቅር ነበር ወላጆቹና ዘመዶቹ የተሻለ ኑሮ እንዲኖሩ የማድረግ ህልም ነበረው ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ከመጣ በኋላ በታላቅ ወንድሙ ምከር የባህር ኃይልን ተቀላቀለሰ በባህር ላይ ይሠራ በነበረበት ጊዜ ምንም እንኳ ብቸኛ ገቢው እርሱ ቢሆንም ይከፈለው ከነበረው ገንዘብ ለቤተሰቦቹ ይልከ ነበር ከጥቂት ዓመታት በኋላ ከእናቴ ጋር ጋብቻው ስለተመቻቸሰለት ለአጭር ጊዜ ወደ ፓኪስታን ተመልሶ ነበር ማ እናቴ ለቤተሰቧና ለሃይማኖቷ የተሰጠ ሕይወት ትኖር ነበር የሙስሊም ሚስዮናዊ ልጅም ነበረች ቋ ባይ ብዬ የምጠራው አባቷ ከእናቷያ ምሳያ ጸማጋር በተጋቡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ኢንዶኔዥያ በመሄድ ሰዎችን ወደ አስልምና ይጋብዝ ነበር ትልቋ እማ ቤተሰቡን ለማኖር ሥራ ትሠራ ስለነበርና ትልቁ አባዬ ደግሞ ብዙ ጊዜ የሚስዮናዊነት አገልግሎቱን ይከውን ስለነበር እናቴ ታናናሾቿን በማሳደግና የእስልምናን መንገድ በማስተማር ትልቅ ሚና ትወጣ ነበር እድሜዋ አሥር ዓመት ሲሆን አማ ከታናናሾቿና ከትልቋ እማ ጋር በመሆን ወደ አገረ ፓኪስታን ተመለሰች የሚስዮናዊነት አገልግሎታቸውን በጥንቃቄ በመወጣታቸውም ምክንያት ማሕበረሰቡ ለቤተሰቧ ሞቅ ያለ አቀባበል አደረገትልቁ አባዬ ግን በኢንዶኔዥያ ውስጥ ሚስዮናዊ ሆኖ በመቆየት ለእረፍት ብቻ ወደ ፓኪስታን ይመለስ ነበርእእማ በቤት ውስጥ ያላት ኀላፊነት ከፍ እያለ መጣ አምስት ታናናሾችዋን የማሳደግ ኀላፊነት ትከሻዋ ላይ ስለወደቀ ሁለተኛ ዲግሪዋን በከፍተኛ ማዕረግ አጠናቃ ሕከምና የማጥናት ዕድል ብታገኝም አልተቀበለችምትልቋ እማ በአካባቢው ጀማት ውስጥ በፍቃደኝነት በጸሐፊነት ታገለግል ስለነበር በቤት እገዛ ያስፈልጋት ነበር ትልቋ እማ ሕይወቷን ከሞላ ጎደል ለእስልምና መስዋዕት ጀማት በአረብኛ ቋንቋ ስብሰባን ቦማድረግ ትኖር ነበር የሚስዮናዊ ሚስት ብቻ ሳትሆን የሚያመለከት ሲሆን እንደ እማ ሁሉ የሚስዮናዊ ልጅም ነበረች አባቷ በሕከምና ብዙ ጊዜ ቡድን ወይም ለብለብ ሶያሰገለ ሰዎችን ወደ አስልምና ይጋብዝ በነበረበት በዩጋንዳ ተብሎ ይተረጎማል ውስጥ ነበር የተወለደቸው የሚስዮናዊ ልጅ ሆና ያደገች የሚስዮናዊ ሚስት ለመሆን የሰለጠነችና የመጨረሻ የሥራ ዘመኗን በጀማት ውስጥ በማገልገል ያሳለፈች በመሆኗ ምከንያት በማሕበረሰቡ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ከበሬታና ተቀባይነትን አትርፋለችትልቋ እማየእናቴ ዋና ሞዴል ነበረች እናቴ ደግሞ ይህንን ቅርስ በራሷ ቤተሰብ ውስጥ ከማስቀጠል የላቀ ሌላ ምኞት አልነበራትም በወቅቱ ለኔ ባይታወቀኝም አዛንን በለሆሳስ በጆሮዬ ላይ የተናገረው ሰው ቁረሺ የሚለውን የከበረ ስም የተሸከመ ራሱን ለሌሎች ሰውቶ የሚኖር አፍቃሪ ሰው ነበር እንከብካቤ ያደረገችልኝ ደግሞ የሚስዮናውያን ልጅ ልምድ ያላት ተንከባካቢና እስልምናን የማገልገል ፅኑ መሻት የነበራት ሴት ነበረች ሁለተኛ ልጃቸውና የመጀመርያ ተባዕት ልጃቸው ነበርኩኝ ወደ ጸሎትአየተጠራሁ ነው ምዕራፍ ሁለት የእናት እምነት በአካል በስሜትና ማሕበራዊ በሆኑ ጉዳዮች ረገድ ይህ ቀረ በማይባል ሁኔታ እንከብካቤ እየተደረገልኝ ነበር የልጅነት ሕይወቴን ያሳለፍኩትሲደረግልኝ የነበረውን ጥንቃቄ ሳስብ እስከ ዛሬ ድረስ አደመማለሁ በሰውነቴ ላይ የሚታዩት ጠባሳዎች አነስተኛ በሆኑ ጉዳቶች የመጡ ምልከቶች ብቻ ሲሆኑ የትላንት ያህል ትዝ ይሉኛል ትልቁ ጠባሳ ይታያችሁ ከሁለት ኢንች አይበልጥም የሦስት ዓመት ልጅ እያለሁ ሰባራ መስኮት እጄ ላይ በመውደቅ ባደረሰብኝ ጉዳት የመጣ ነበር ያ ዕለት በአእምሮዬ ውስጥ ተቀርፆ የቀረው ስለ እናቴ እምነት ካወቅሁት ነገር የተነሳ ነው በወቅቱ አባቴ በኖርፎልከ ቨርጂንያ ውስጥ ተመድቦ ይሠራ ነበር ባሕር ኃይልን ከተቀላቀለ አስራ አንደኛ ዓመቱን የያዘ ሲሆን ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ቀን ቀን እየሠራ ማታ ማታ ደግሞ ሁለተኛ ዲግሪውን ያጠና ነበር ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላ ከተራ አባልነት ከፍ በማለት የደረጃ ሁለት ሌውትናንት ማዕረግ አግኝቶ ነበር በአርግጥ በወቅቱ ብዙም የማውቀው ነገር አልነበረኝም የማውቀው ብቸኛ ነገር ቢኖር አባዬ ስለ እኛ በትጋት መሥራቱን ነው ከዚህ የተነሳ ፍቅር ባይጓደልብኝም ነገር ግን ብዙ ጊዜ አላየውም ነበር አማ ዘወትር የማትለየን ተንከባካቢያችንና በሕይወታችን ውስጥ የጎላ ተፅዕኖ የነበራት አሳዳጊያችን ነበረች ዘወትር ሁሉንም ነገር ማድረግ የምትቸል ትመስል አቂዳ ጥልቅ የሆኑ ነበርሔምግባችንን ከማዘጋጀት ጀምሮ ልብሳችንን በንፅህና አስላማዊ እምነቶች አእስከመጠበቅ ከዚያም አቂዳ አስከማስተማር ድረስ የሚገኙትን ጉዳዮች ስትከውን የድካም ስሜት የሚሰማትም አይመስልም ነበር አንድም ቀን ስትማረር አይቻት አላውቅምነገር ግን አእምሮዋን እንዳትስት በጣም ጠንካራና የማይለዋወጡ ሁለት ሕግጋት ብቻ ነበሯት ማታ ከሦስት ሰዓት በኋላ ምንም ዓይነት መነጫነጭ የለም እንዲሁም ብዙ ጊዜ እንደምታደርገው ሻይ በምትጠጣበት ጊዜ መረበሽ አይቻልም የሚሉት ነበሩ እንግዶቻችንን ተቀብሎ ማስተናገድ ከብር ነው የሚል እምነት ስለነበራት እንግዶች በሚመጡበት ጊዜ ከፍተኛ የሆነ ደግነት ታሳይ ነበርእንግዶቹ መብላት ከሚችሉት በላይ ምግብ ይዘጋጃል ቤቱ ከተሰራበት ቀን ይልቅ ይፀዳል ሽከ ብለን እንለብሳለን መርሃ ግብራችን በዚያን ዕለት ነፃ ይሆናል ምናልባት አንግዳው መቆየት የሚፈልግ ከሆነ ተብሎም አንድ ተጨማሪ ቀን ነፃ ይደረጋል እንዲህም ሆኖ ምግብ ባለመኖሩና እኛም ደግሞ በጥሩ ሁኔታ ባለመልበሳችን እንግዳውን አብዝታ ይቅርታ መጠየቅ የመስተንግዶው አካል ስለነበር ለምደነዋል እንግዶቹም መልሰው አንዲህ ዓይነት አጅ የሚያስቆረጥም ምግብ ከበሉ ዓመታት ማለፉን አንዲህ የፀዳ ቤት በሰማይ እንኳ መኖሩን እንደሚጠራጠሩና እኛ ልጆቿም ለልጆቻቸው ጥሩ ምሳሌ የምንሆን መሆናችንን ይነግሯት ነበር በዚህ ጊዜ ሁሉም ሰው የኩራት ስሜት ይሰማዋል አንግዶቹ ከበሬታን በማግኘታቸው እማ በመወደሲና እኛ ህፃናት ደግሞ በአዋቂዎች ንግግር መካከል ስማችን በመጠቀሱ አንዳንዴ እንግዶቹ ለወራት ያህል ከእኛ ጋር የሚቆዩ ቢሆኑም የእማ ደግነት ግን ፈፅሞ አይነጥፍም በቤታችን ረጅሙን ጊዜ ከሚያሳልፉት እንግዶች መካከል ትልቋ እማና ማግ ብለን የምንጠራት እህቷ ይጠቀሳሉ እማማ ልበ ሰፊ በጣም ሳቂታና ትንሽ ሰውነት የነበራት ፍልቅልቅ ሴት ነበረችከኔ ጋር የገበታ ጫወታዎችን ለመጫወት ምን ጊዜም ዝግጁ ስትሆን ለሦስት ዓመት ልጅ የሚያስፈልገውን ታጋሽነት አታጎድልም ነበር እኔ ሳጭበረብር ደግሞ አውቃ ማዶ ማዶ እየተመለከተች ያላየች ታስመስል ነበር የመቁሰል አደጋው በደረሰብኝ ዕለት አማማ እቤታችን ነበረች አርሷና አማ የላይኛው ከፍል ውስጥ የነበሩ ሲሆን እኔ ደግሞ እማ በገበያ አዳራሾች ውስጥ እንዳልረብሻት ለማባበያ በገዛቸልኝ መንሸራተቻዎችና ትንንሽ የመጫወቻ መኪኖች አየተጫወትኩ ነበር ታላቅ አህቴ ባእና አኔ ጥሩ መግባባት ነበረን በእርሷ ትንንሽ ፈረሶች የምጫወት ከሆነ እርሷ ደግሞ ከእኔ ጋር ሆና በኔ መንሸራተቻዎች ትጫወታለችየምትፈልገውን መኪና መርጣ ትወስዳለች እኔም ደግሞ የምፈልገውን ፈረስ መርጩ አወስዳለሁ አሻንጉሊት ፈረሶቿን በኩራት ሄጄ በመውሰድ የተሻለውን መርጩ መውሰዴን ተከራክሬ አሳምናታለሁ ብዙ ጊዜ አንድ ዓይነት መኪና መርጣ የምትወስድ ሲሆን አርሷ ያልወሰደችው በእጄ የሚገኘው መኪና የተሻለ መሆኑን ተከራከሬ አሳምናታለሁ ባጂ በመንሸራተቻዬ ተጫውታ ሰልችቷት ፈረሶቿን ለመውሰድ ሄዳለች እኔ ደግሞ መኪናዬ ላይ ተቀምጩ ወለሉ ላይ በአግዳሚ ወንበሮች መካከል እየበረርኩ መጫወቴን ቀጥያለሁ በከፊል የተከፈተውን መስኮት ቀና ብዬ ተመለከትኩት ከዚያም መኪናውን ለማጋጨት ጊዜው አንደሆነ አሰብኩኝ መኪናውን ወደ መስኮቱ እያበረርኩኝ በመውሰድ ከመስታወቱ ጋር አጋጨሁት እስከ ዛሬ ድረስ የመስኮቱ አወዳደቅ ትዝ አይለኝም የማስታውሰው ነገር ቢኖር ሰቅጣጭ የሆነውን ህመም የማያቋርጠውን ደምና የአምባ ዶፍ እያዘነብኩኝ እማን ጮኬ መጣራቴን ነው እማ ከደረጃው ላይ በጥድፊያ ወርዳ በመምጣት አደጋውን በተመለከተች ጊዜ ለማልቀስ ምንም አልቀራትም ነበር ነገር ዱዓ በተወሰኑ ጊዜያት የሚደገሙ የሙስሊም ግን ወዲያውኑ ስሜቷን ተቆጣጠረች የባሕር ኃይል ፀሎቶች ሲሆኑ ከሰላት የተለዩ ናቸው መኮንን ሚስት እንደመሆኗ መጠን የ ያበዱ በራስ አባባል የሚፀለዩ ሊሆኑ ይቸላሉ የእናትነትንምየአባትነትንም ሚና መጫወት ታውቅበታለች አሁን ደግሞ ጊዜው የማልቀስ አይደለም ነገር ግን ማድረግ የሚገባትን በብልሃት እያደረገች ፍርሃቷን ለአላህ ሰጠቸው መስኮቱን ካነሳች በኋላ አጄን በፋሻ በመጠቅለል ሁርቃዎ። በማለት ብዙ ጊዜ ታዛዥነትን ታስታውሰኝ ነበር ኋላ ላይም ጌታ ኢየሱስን ለመከተል ሳስብ ትልቅ አለመታዘዝ የሆነውን ውሳኔ ልወስን እንደሆነ ስለተሰማኝ ውስጤ ተረብሾ ነበር ቤተሰቦቼ እንደተከዱ ብቻ አይደለም የሚሰማቸው ነገር ግን ልባቸው ሊጠገን በማይችል ሁኔታ ይሰበራል ነገር ግን የአራት ዓመት ልጅ እያለሁ ስለ ልብ ስብራትና ቤተሰቦቼን ስለማሳዘን ማሰብ አልችልም ባለ እንጆሪዋ ወንበሬ እንድትመለስልኝ ብቻ ነበር ፍላጎቴ ሁሉም ነገር ተሸከኖ ለጉዞ ዝግጁዎች ከሆንን በኋላ አባዬ ቤተሰቡን በመሰብሰብ እስቲ እንጸልይ አለ እማና አባዬ እንደሚያደርጉት ሁሉ መዳፎቼን ቆልመም በማድረግ ወገቤ አካባቤ ከፍ አደረኳቸው ሁላችንም በዝምታ ጉዚችን መልካምና የቀና እንዲሆን አላህን ለመንነው ወደ አባዬ አዲሱ የምድብ ቦታ ስንደርስ በዱኑን ስኮትላንድ ውስጥ ራሳችንን አገኘን አሁን ዞር ብዬ ሳየው ዱኑን የመጀመርያው ትከከለኛ ቤቴ እንደነበር ይሰማኛል በትምህርት ቤት ብዙ ጓደኞችን ስላፈራሁ ወይም ብዙ የጎረቤት ልጆችን ስለተዋወቅሁኝ አልነበረም ባለ እንጆሪዋ ወንበር እንኳ ተወስዳብኛለች ነገር ግን በነዚያ ዓመታት ከቤተሰቤ ጋር በጥብቅ ስለተቆራኘሁና እምነቴን በጥልቀት ስላወቅሁ ነው እናቴ አባቴና እህቴ ነበሩኝ ከእነርሱ ውጪ ሴላ አያሻኝም ነበር ምዕራፍ አራት ፍፁም የሆነው መጽሐፍ ስኮትላንድ በደረስኩ ጊዜ እንግሊዘኛን በሚገባ አልተማርኩም ነበር በቤት ውስጥ የምንነጋገረው በኡርዱ ብቻ ሲሆን የምንማራቸው ፊደላት ደግሞ የአረብኛ ብቻ ነበሩ ይህ የሆነበት ምከንያት ግልፅ ነውቁርአን በአረብኛ ስለተጻፈ እኔና ባጂ ለማነብነብ መማር ግድ ስለሆነብን ነበር ሙስሊሞች እያንዳንዱ የቁርአን ቃል ከአላህ ዘንድ በመልአኩ ገብርኤል አማካይነት ለመሐመድ ቃል በቃል እንደተነገረው ነው የሚያምኑት ስለዚህ ቁርአን በትርጉም ደረጃ ብቻ ሳይሆን ቃላቱ አንኳ በቀጥታ ከሰማይ የመጡ መገለጦች ናቸው ከዚህ የተነሳ ሙስሊሞች ቁርአን ሊተረጎም እንደሚችል አያምኑም ከአረብኛ ውጪ ባለ በሌላ በየትኛውም ቋንቋ ቢጻፍ ቁርአን ሳይሆን የቁርአን ፍቺ ነው የሚሆነው መጽሐፉ እውነተኛ ቁርአን የሚሆነው በአረብኛ ሲጻፍ ብቻ ነው ለዚህ ነው ቁርአን ቃል በቃል ነቁጥ በነቁጥ ሳይለዋወጥ አንደቆየ ማመን ለሙስሊሞች አስፈላጊ የሆነው ኢማሞችና አስተማሪዎች ብዙ ጊዜ መሐመድ ከገብርኤል ከሰማበትና ለጸሐፍቱ ካነበነበበት ጊዜ ጀምሮሳይለዋወጥ በትከከል ተጠብቆ መቆየቱን ይናገራሉ በአርግጥ መሐመድ ኤ ቁርአንን በማቀናበር ረገድ ምንም ያደረገው ነገር አልነበረም እርሱ መገለጡን ለሰው ልጆች የሚያደርስ ማስተላለፍያ ብቻ ነበር ትክከለኛ መልኩንም ኀላፊነት በተሞላበት ሁኔታ ጠብቋል ይህንን ባያደርግና ቃላቱ ትንሽ አንኳ ቢለወጡ ኖሮ ቁርአን ዳግመኛ ሊገኝ በማይችልበት ሁኔታ በጠፋ ነበር ነገር ግን ቃላቱ ተለዋውጠዋል ብሎ ማሰብ የማይቻል ነው ቁርአን እንከን የለሽ በሆነ ሁኔታ መተላለፉን የሚጠራጠር ማንም የለም ስለዚህ የቃላቱ እንከን አልባ መሆን ጥርጥር የለውም በእርግጥ ቃላቱ ላይ ትኩረት በማድረጋቸው ምከንያት ብዙ ሰዎች የቃላቱን ትርጉም ችላ ብለዋል ቁርአንን በየጊዜው የሚያነበንቡ ሰዎች ብፁዓን ተደርገው የሚቆጠሩ ሲሆን በቁርአን ትርጉም ላይ ብቻ የሚያተኩሩ ሰዎች ደግሞ ምሑራን ተደርገው ይታሰባሉ ብፅዕና ትልቅ ከብር በመሆኑ ምከንያት እኔ የማውቃቸው ብዙ ሰዎች የቁርአንን ብዙ ከፍሎች በቃላቸው ሸምድደው ቢይዙም ነገር ግን የአንቀፆቹን አውድ ወይም ትርጉም እምብዛም ማብራራት አይችሉም እማ የቁርአንን መነባንብና ፍቺ ታስተምረን ነበር ነገር ግን ማነብነቡን ታስቀድም ነበር በየዕለቱ ባሕላዊውን የሙስሊም ኮፍያ አራሴ ላይ በመድፋት ከአጠገቧ አስቀምጣ አረብኛ ታስጠናኝ ነበርዳቃዲ መመርያ በሚል መጽሐፍ ነበር የጀመርነው የአረብኛን ፊደሎች የተለያዩ መልኮች ከነድምፆቻቸው ተምረንበታል ልከ ስኮትላንድ ከመድረሳችን ተመርቄ ከቃኢዳ ወደ ቁርአን ተሻገርኩኝ ያቺ ዕለት በጣም ትዝ ትለኛለች ምከንያቱም በሕይወቴ በጣም ከደነገጥኩባቸው ቀናት መካከል አንዷ ነበረችና የመጨረሻውን የቃኢዳ ገፅ አጥንቼ ስጨርስ አማ በአጠገቧ የተቀመጠውን ቁርአን አንስታ በስጦታ መልክ አበረከተችልኝ ይህ ቁርአን አንደ ስጦታ የተቀበልኩት የመጀመርያው መጽሐፍ ነበር እየፈነደቅሁኝ ለባጂ ላሳያት በርሬ ሄድኩኝ ባጂ በአባና እማ ከፍል ጎን ወለል ላይ ትጫወት ስለነበር አጠገቧ ቁጭ ብዬ ቁርኣኑን ላሳያት መሬት ላይ አስቀመጥኩት ከመቅፅበት አማ ጆሮን የሚበጥስ ጩኸት አያሰማች ወደኔ አቅጣጫ እየተደነቃቀፈች መጣቶ ኀቢል ብላ አምባረቀች ድርቅ ብዬ ቀረሁ እንደዚያ ስትጮኸም ሆነ ስትጣደፍ አይቻት አላውቅም ነበር ቁርአንን መሬት ላይ አታስቀምጥ እሺ ሁል ጊዜ ከፍ አድርገህ ያዘው ከፍ ባለ ቦታ ላይ አስቀምጠው ከመንካትህ በፊት እጅህን ታጠብ በቀኝ አጅህ ብቻ ያዘው ይህ አንደማንኛውም መጽሐፍ አይደለም የአላህ ቃል ነው ተገቢ የሆነውን ከብር ስጠው እሺ ሂድ በጣም ተበሳጭታ ስለነበር ሳላቅማማ ሱልል ብዬ ሄድኩኝ ከዚያን ዕለት ጀምሮ ቁርአንን ከፍ አድርጌ መያዝ ጀመርኩኝ ባጂም ከኔ ስህተት ተምራ ስለነበር በሚቀጥለው ጊዜ እማ ቁርአኖቻችንን አምጥተን እንድናነብ ስትነግረን እጆቻችንን የቻልነውን ያህል ወደ ላይ በመወጠር ከራሶቻችን በላይ ከፍ አድርገን በመያዝ መጣን እማ ፈገግ አለች ለማለት የፈለገችው እንደርሱ ባይሆንም ነገር ግን ደስተኛ ነበረች ባጂ ታላቅ እንደመሆኗ መጠን ቀደመቸ አማ ባጂ የምታነባቸውን ቃላት በጣቷ እየጠቆመች በገፁ ላይ በቀስታ ከግራ ወደ ቀኝ ታንቀሳቅስ ነበር ባጂ ቃላቱን በዜማ ስትላቸው ስለነበር በፍጥነት አታነብም ነበር ቁርአንን በዜማ እንድናነብ ነበር የተማርነው ድምፁንም የተቻለንን ያህል ለማስዋብ ጥረት እናደርግ ነበር አንዳንድ ሰዎች ቅኝታቸውን ምታቸውን የድምፅ አወጣጣቸውንና ዜማቸውን በማስተካከል ለዚህ ልምምድ ሕይወታቸውን ይሰጣሉ ነገር ግን እኔና ባጂ አንደዚያ አልነበርንም ጥቂት ዓመታትን ከኔ ቀደም ብላ የጀመረች ስትሆን በመጠኑ ቁርአንን ማነብነብ ተምራለች እኔ ከዚያ ቀደም ቁርአንን አንብቤ ስለማላውቅ በጣም ጓጉቼ ነበር ቢሉ ከሁሉ አስቀድመን የምናነበንበው ምንድነው። ለዚህ ነው ዛሬ የሚገኘውን መጽሐፍ ቅዱስ ማመን የማንችለው ተበርዚል ትከከለኛው ቁርአን ብቻ ነው እስልምና ብቻ ነው መበረዝ የማይችለው መልእከቱ እስኪሰራጭና መላው ዓለም ሙስሊም እስኪሆን ድረስ አላህ ይጠብቀዋል ያ የፍርድ ቀን የሚመጣበት ነው ያ እስልምና ድል ነሺ የሚሆንበት ዕለት ነው አባዬ ለአምነቱ ባለው ፍቅር ሁላችንም ደስተኞች ነበርን ለመጪው ዓለም አቀፋዊ እስላማዊ የበላይነት ያለውንም ራዕይ ተቀብለናል ይህንን ድል ነውጠኛ የሚያደርገው ምንም ነገር የለም ይህ የሚያማልል ዓይነት አፈፃፀም ነው እንዲህ እንዲህ እያልን ለጥቂት ጊዜ በምናብ ከተንሳፈፍን በኋላ እማ ወደ ምድር መለሰችን ቻሎ ይህ በቂ ነው ከአፍታ በኋላ መስጊድ እንደርሳለን እንዘጋጅ ትከከል ነበረች ወደ መስጊድ እየቀረብን ነበር ጊዜ ራሱ የቆመ ስለመሰለኝ ከመርከቢቱ ላይ ስንወርድ እንኳ አልታወቀኝም ነበር ስለ ሃይማኖት መወያየት በጣም ያስደስተኛል ቁርአን አላህ መሐመድ ቀናት ስሞች ቦታዎች ሁላቸውም ቀልቤን ይስቡት ነበር ስለ መጽሐፍ ቅዱስና ስለ ኢየሱስ ማውራት እንኳ ያስደስተኝ ነበር በኔ ፅይታ ይህ ሁሉ አላህ ለሰው ልጆች ያቀደውና በምድር ላይ ከኖሩት መካከል ታላቁ ሰው በሆነው በመሐመድ በኩል እውን የሆነ አቅድ እንደሆነ ይሰማኝ ነበር ልባችንን ለአርሱ ሰጥተናል ከእርሱም ጋር ቃልኪዳን አድርገናል ምዕራፍ ስድስት በጸሎት ሥርኣት የሚገኝ ፅድቅ ልጅ ሳለሁ የግላስጎው መስጊድ ከምወዳቸው ቦታዎች መካከል አንዱ ነበር ከአውራ ጎዳናው ትንሽ ፈንጠር ብሎ ባልተለመደ አቀማመጥ በከሊድ ወንዝ አጠገብ ይገኛል በቀይ ድንጋዮች የተሰራና አረንጓዴ ጣርያ እንደ ኮፍያ የደፋ ሲሆን በስርኣት ያልተደረደሩ መወጣጫዎች ያሏቸው ብዙ ወለሎች በሮችና መተላለፍያዎች ነበሩት ከሌሎች ሙስሊም ልጆች ጋር አኩኩሉ ለመጫወት አመቺ ቦታ ነበር ከልጆች ጫወታ በተጨማሪ ብዙ የምዕመናን ከንዋኔዎች በመስጊዱ ውስጥ ይታዩ ነበር ለዓመት በኣላት ለከብረ በኣላት ለቀብር ሥርኣቶች ለሠርግ ለሽርሽር ለመዝናናትና ለሌሎችም ብዙ ጉዳዮች እንደ ማሕበረሰብ እንሰበሰብ ነበር መስጊድ ለሙስሊሞች በተለይም ደግሞ ከአገር ቤት ርቀው ለሚኖሩ ሕብረት ለናፈቃቸው ሙስሊሞች በጣም የተወደደ ቦታ ነው ነገር ግን ከነዚህ መካከል አንዱ እንኳ የመስጊድ ዋነኛ ዓላማ አይደለም ሰላት የሙስሊሞች የመስጊድ ዋና ዓላማ የጋራ ጸሉት ሰላት ነው እነዚህ ሥርኣታዊ ጸሎት በቀን አምስት ጊዜ በሙስሊሞች የሚፈፀሙ የግዴታ ጸሎቶች ናቸው መጀመርያ እንቆማለን ከዚያ እናጎነብሳለን ከዚያ ለአጭር ጊዜ በግንባራችን መሬት ላይ እንደፋለን ከዚያ ቀና በማለት ተረከዛቾን ላይ እንቀመጣለን በአረብኛ የተሸመደዱ ጸሎቶችንም ወደ አላህ እንጸልያለገ እያንዳንዳቸው አምስቱ የዘወትር ጸሎቶችየየራሳቸው ስም አላቸው ፈሯረና ያዝሠር መግሠ ና ፈቻ ቃላትና አሰጋገዶች ለሁሉም አንድ ቢሆኑም ነገር ግን የድግግሞሽ ልዩነት አላቸው እያንዳንዱ ድግግሞሽ ረካት በመባል ይታወቃል አንድ ሙስሊም በቀን አስራ ሰባት ረካት መጸለይ ይጠበቅበታል አማራጭ ጸሎቶችቸም ጎን ለጎን ይደረጋሉ በኛ ጀማት ከተቻላ በየዕለቱ ሠላሳ አንድ ረካት አንድንጸልይ ተምረናል የጸሎት ሰዓታት ለሙስሊሞች የየዕለት የሰዓት አከፋፈል በመሆን ያገለግላሉ አዛን ለፈጅር ያነቃናል ለዙሁር ከረፋዱ ሥራችን አረፍ እንላለን ከአስር በኋላ ወደ ቤታችን እንሄዳለን ከመግህሪብ በኋላ አራት እንበላለን ከኢሻ በኋላ ደግሞ ለመኝታ እንዘጋጃለን ልከ አዛን እንደተሰማ እነዚህን ጸሎቶች ከመፈፀማቸው በፊት ሙስሊሞች ውዱበመባል የሚታወቅ የትጥበትሥርኣት ይፈፅማሉ ይህም ሥርኣታዊ የእጅ የፊትና የእግር ትጥበት ነው ውዱ በሚፈፅሙባቸው ጊዜያት የተሸመደዱ ዱኣዎችን ይጸልያሉ ከዚያም በጥድፊያ ወደ ጸሎት ስብሰባው ይሄዳሉ በመላው ዓለም የሚገኙት ሙስሊሞች ከሞላ ጎደል ረካት በመቆም ተመሳሳይ በሆነ ሁኔታ ይጸልያሉ በርግጥ ለጸሎት ማጎንበስ መስገድ እና በሚቆመበት ሰዓት ሁላቸውም ጥቁር አራት ጎን መቀመጥ የጠከፋለ ሸን ወደሚመስለው ከዕባ ወደተባለው የሙስሊሞች የተቀደሰ ቦታ ፊታቸውን በማዞር ነው በሙስሞች አፈታሪከ ውዱ ከሰላት በፊት ጩራረት ካዕባን የሰሩት አብርሃምና ልጁ እስማኤል የሚደረግ የመታጠብ ሥርአት ነበሩ መሐመድ ወደ መዲና ከተሰደደ በኋላ ሙስሊሞች ሁሉ በሰላት ሰዓት ወደ ካዕባ እንዲዞሩ ኢማም ብዙ ጊዜ በመስጊድ ፀሉትን ሶቧቸዋል ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ካዕባን በከበበው ዋናው የሚመራ የሙስሊሞች መስጊድ ውስጥ ሲቆሙ ከብ በመስራት እንዲሁም ቤ በመላው ዓለም በረድፍ በመቆም ስግደታቸውን ይፈፅማሉ በምዕራብ የሚኖሩ ሙስሊሞች ትከከለኛውን አቅጣጫ ለማወቅ ኮምፓስ ሲጠቀሙ ሳታዩ አትቀሩም ኮምፓስ የተገጠመላቸው የጸሎት ከፍሎችን እንኳ አይቻለሁ ጸሎቱ ኢማም በተባለ አንድ ሰው ይመራል ሴቶችና ወንዶች በተለያዩ ከፍሎች ውስጥየሚሜጸልዩ ቢሆኑም ነገር ግን የኢማሙን ድምፅ መስማት በሚችሉበት ርቀት ላይ ይሆናሉ ኢማሙ ሲመራ የተወሰኑ የጸሎቱ ከፍሎች በዝምታና በግል ይጸጻጸለያሉሱ ሌሎቹን ደግሞ ኢማሙ ድምፁን ከፍ በማድረግ ይናገራቸዋል እያንዳንዱ የጸሎቱ ከፍል በቁርአን ንባብ የታጀበ ሲሆን ኢማሙ ሁልጊዜ እነዚህን በቃል ያነበንባቸዋል በጸሎት ሰዓት ቁርአንን ማነብነብ በሰባተኛው ከፍለ ዘመን ይኖር በነበረው በአብዛኛው ፊደል ባልቆጠረው ማሕበረሰብ መካከል ቁርአንን ለማስተማር የተዋጣለት መንገድ የነበረ ሲሆን ይህ ዘዴ ዛሬም ድረስ ይሠራል ለዚህ ነው አንድ ሰው ኢማም ለመሆን የሚያስፈልገው ብቸኛ መመዘኛ ቁርአንን ማወቅና አብዛኛውን ከፍል በቃል ማነብነብ የሆነው አልፎ አልፎ ኢማሙ ሲያነበንብ ሳለ ስህተቶችን ሲሰራ ይትላል ይህ በሚሆንበት ጊዜ ማስተካከያ መስጠት ከፊት የሚቆሙት ሰዎች ኃላፊነት ነው የሚሆነው ከዚህ የተነሳም በሰላት ሰዓት ከፊት የሚቆሙት ሰዎች በእድሜ ጠና ያሉ የተከበሩ ሙስሊሞች ሆነው ይታያሉ ከዚህ አነስተኛ ሁኔታ በተረፈ ሙስሊሞች በሰላት ጊዜ በሚኖረው እኩልነት ኩራት ይሰማቸዋል ከባለጠጎች ጀምሮ እስከድሆች ከመሪዎች እስከ ተራ ሰራተኞች ድረስ ሁሉም ሰው ጎን ለጎን ቆሞ በአንድነት ይጸልያል ማንም የማይናገርበት በጸላዮች ፊት የማያቋርጥበት ማንም ጣልቃ የማይገባበት ከቡር ሥርኣት ነው በእርግጥ ከአምስት አመት ቀዥቃዣ አሜሪካዊ ህፃን በስተቀር ይህንን ለማድረግ የሚደፍር ማንም የለም በሰላት ሰዓት በጸላዮቹ መካከል ስሽሎከሎከ ከድርጊቴ እንድታቀብ የሆነ ሰው በስሱ ኩርኩም ያቀምሰኝ ነበር ወላጆቼ በዚህቅሬታ አይገባቸውም ነበር አንድን ህፃን ማሳደግ የመስጊዱ ሁሉ ኃላፊነት እንደሆነ ስለሚታመን የኛ ጀማት አባላት ጥልቅ የሆነ መተማመን ነበራቸው ከዕለታት በአንዱ ቀን አንደ ልማዴ በሰላት ሰዓት ያለ አረፍትስሯሯጥ አንድ እጅ ከበስተጀርባዬ ቸብ ሲያደርገኝ ተሰማኝ ማን እንደመታኝ ለማየት ዘወር ብል ማንንም ማየት አልቻልኩኝም በቅርብ ርቀት ላይ የነበረው አጎቴ ስለነበር እርሱ አንደመታኝ በማሰብ የሰላት ሰዓቱ ሲያበቃ አምባ እያዘራሁከሰስኩት ፊቱ ላይ ምንም ምልከት ሳያሳይ ጣቱን ወደ ሰማይ በመቀሰር አላህ ነው የመታህ አለኝ ከዚያም በመገረም ወይኔ በፍጥነት ዘወር ብዬ ቢሆን ኖሮ የአላህን እጅ ለጥቂት አይቼ ነበር ብዬ አሰብኩኝ ከዚያን ቀን ጀምሮ በሰላት ሰዓት አደብ ገዝቼ መቆም ጀመርኩኝ ከሃያ ዓመታት በኋላ አጎቴ እንደመታኝ ቢናዘዝም አስከዚያችዕለት ድረስ ግን በአላህ በራሱ እጅ በመመታቴ ኩራት ይሰማኝ ነበር ቃላቱና አቋቋሙ ሁሉ የተሸመደዱ ስለሆኑ ሰላትን ግላዊ የሚያደርገው ምንም ነገር የለም ለአብዛኞቹ ሙስሊሞች የግዴታ ተግባር እንጂ ግላዊና ልባዊ አይደለም አንድ ሰው የሚያነበንባቸውን ቃላት ትርጉም እያሰበ በመጸለይ ግላዊ ሊያደርገው ቢችልም ነገር ግን በየዕለቱ አስራ ሰባቱንም ረካቶች በዚያ መልኩ የሚተገብር ሙስሊም አይኖርም ቃላቱ ራሳቸው በባዕድ ቋንቋ በመሆናቸው ምከንያት አነብናቢው ሊያሰላስላቸው አይችልም ይህ ለአረብኛ ተናጋሪዎች እንኳ እውነት የሆነ ጉዳይ ነው አረቦች ከቦታ ቦታ የሚለያዩ የተለያዩ ዘዬዎች ያለውን አረብኛ ነው የሚናገሩት የጥንቱን አረብኛ የሚማሩት በትምህርት ቤት ነው የዘወትር ጸሎት ቋንቋ የማንም አይደለም እውነቱ ይህ ሆኖ ሳለ ሙስሊሞች ለምን በቀን አምስቴ እንደሚጸልዩ በማሰብ ግራ የሚገባው ሰው ሊኖር ይችላል ለግላችን ምንም ትርጉም የማይሰጡን ከሆነ ተመሳሳይ ቃላትን በቀን አምስቴ ማነብነቡ ትርጉሙ ምንድነው። ይህንን ሰይጣን አንኳ ማሰናከል አይቻለውም ሚስዮናዊው ይህንን በተናገረ ጊዜ ቅፅበታዊ ጩኸቶች ከሕዝቡ መካከል ተዥጎደጎሩቶ ሁሉም አንድ ነገር ነበር የሚሉት ተከቢር በድንኳኑ ውስጥ የተሰበሰቡት በሺህዎች የሚቆጠሩት ሰዎች በአንድ ድምፅ ምላሽ ሰጡ አላሁ አከበር ጠንከር ያለው ድምፅ በድጋሚ አሸንፎ ወጣ ተከቢርየተሰበሰቡት ወንዶች ሁሉ በጋለ ስሜት መልስ ሰጡ አላሁ አከበርአሕመዲዎች መስማማታቸውን ለመግለፅ ብዙ ጊዜ አያጨበጭቡም ነገር ግን አላህን ለማመስገን ና በረከቱን ለመለማመን አንዳቸው ሌላቸውን ይቀሰቅሳሉ ተከቢር በማለት የጮኸው ሰውዬ አሁንም እስላም በማለት ጩኸቱን ቀጠለ መልሱም ቆፃፀድ ለዘላለም ይኑር የሚል ነበር እስላም ዚንዳባድይ አሕመዲያ ዚንዳባድ ተለይተው የማይታወቁ ድምፆች በመብረቅ ጩኸት የሙስሊሙን ሰራዊት አላህን እንዲያወድሱ ሲመሩለተመለከተ ሰው ጊዜ ራሱ የቆመ መስሎ ሊታየው ይችላል በርግጥ ከዳር ሆኖ ለሚመለከት ሰው ሰራዊቱ ከሰላማዊ ሙስሊሞች የተዋቀረ መሆኑ ሊገባው አይችልምበሺዎች የሚቆጠሩት ሰዎች ማጓራት እጅግ አስደንጋጭ ነበር ምንም ነገር ሳይጨምር ሚስዮናዊው ጉባኤውን በማመስገን ንግግሩን ቋጨ ዛሬ ላይ ደርሼ የትከከለኛነትና የስህተት ትምህርት ተከታይነት ብዙ ገፅታዎች ያሉትና ውስብስብ መሆኑን ተረድቻለሁ በዚህ ዘመን ከጥቃቅን ነጥቦች በመነሳት ብዙ ሙስሊሞች አንዳቸው ሌላቸውን ሙስሊም እንዳልሆኑ መናገራቸው እውነት ነው እዚህ ግቡ በማይባሉ አለመስማማቶች ሳብያ ከሃዲ ተባብሎ መፈራረጅ የተለመደ ነው ከእነዚህ ሁሉ የእስልምና አንጃዎች መካከል የከሃዲነት ታርጋ ያልተለጠፈበት አንድ ቡድን እንኳ መኖሩን እጠራጠራለሁ ይህ እንዳለ ሆኖ የአሕመዲያዎች መስራች ብዙ ወገኖችን ሊያስቆጡ የሚችሉ ነገሮችን ስለ ራሱ ብሏል እርሱ የኢየሱስ ዳግመኛ ምፅዓት መሆኑን መናገሩ ከርስቲያኖችንም ሆነ ሙስሊሞችን ማስቆጣቱ አሙን ነው ለነቢያት የሚገባውን ከብር መጠየቁ በሙስሊሞች ዘንድ በቀላሉ የሚታይ አይደለም ትከከለኛ ሙስሊሞች የሚባሉቱ አሕመዲያን አንደ ምንፍቅና መቁጠራቸው ለምን እንደሆነ ማየት አያዳግትም ነገር ግን ለእኔ አሕመዲያዎች ሙስሊሞች እንደሆኑ እንዳምን የሚያደርጉኝ ብዙ ምከንያቶች አሉ ሚስዮናዊው አንደተናገረው አሕመዲያዎች ዋና ዋና የሚባሉትን የእስልምና አስተምህሮዎችና ልምምዶች ሁሉ ይተገብራሉ የየዕለት ኑሯቸውና በተግባር የሚገለፀው አምነታቸው ሲታይ አሕመዲያዎች ከሞላ ጎደል ከሱኒ ሙስሊሞች የተለዩ አይደሉም በተመሳሳይ ሁኔታ እኔ ራሴ አሕመዲ በነበርኩበት ዘመን ሙስሊም መሆኔ እንጂ አሕመዲ መሆኔ ብዙም አይሰማኝም ነበር ነገር ግን ከዚህ በላይ መሐመድ አራሱ አሕመዲዎችን እንደ ሙስሊም ይቆጥራቸዋልከአላህ በስተቀር አምላከ አለመኖሩን የሚያውጀውን ሰው ከማሕበር አታግልሉት ብሏል ከዚህ መማር ያለብን ነገር ቢኖር በእስልምና ውስጥ ብዙ ከፍፍል መኖሩን ነው አንድ ሰው ሙስሊም መሆኑን ለማወቅ እንደ መመዘኛ የሚጠቅመው አላህ አምላከ መሆኑንና መሐመድም መልእከተኛው መሆኑን ማወጁ ነው ከዚህ ነጥብ ባሻገር ባሉት ጉዳዮች ላይ በእስልምና ውስጥ ብዙ መከፋፈል አሰ ምዕራፍ ስምንት ፍኖተ ሸሪኣ ሸሪኣ ሲነሳ በእስልምና ውስጥ ከሚገኘው ብዝሃነት ጋር የተያያዙ ብዙ አመለካከቶችን እናገኛለን ሸሪኣ አብዛኞቹ ሙስሊሞች በጥልቀት የሚያውቁት ዘርፍ አይደለም ይህንን ቃል ለመጀመርያ ጊዜ የሰማሁት የኛ ጀማት በዓመት አንድ ጊዜ በሚያዘጋጀው ፌቻዖማወይም የውድድር መርሃ ግብር ላይ ነበር ውድድሮቹ መንፈሳዊና እስፖርታዊ ገፅታዎችነበሯቸው መንፈሳዊ ገፅታዎቹ የቁርአን ሽምደዳ ቁርአንን ማነብነብ የአዛን ከህሎት አስላማዊ ግጥሞችን ማነብነብ የንግግር ውድድር የሐዲስ ሽምደዳ እና ጠቅላላ የሃይማኖታዊ አውቀት ፈታናዎችን ያጠቃልላል አማ በመንፈሳውያኑ በተለይም ደግሞ የንግግር ውድድር ላይ እንዳተኩር ታደርግ ስለነበር እስፖርታዊ ውድድሮቹ ምን ምን አንደሚያጠቃልሉ የማውቀው ነገር የለኝም እማ ለንግግር አንድዘጋጅ በጥብቅ ታሰለጥነኝ ነበር ንግግሩን በሙሉ ከመጻፍ አልፋ እንዴት ማቅረብ እንዳለብኝ አሰልጥናኛለች ከውድድሩ ቀደም ብለው በነበሩት ምሽቶች ከኢሻ ሰላት በኋላ ቆሜ እንድለማመድ ታደርግ ነበር ከበስተጀርባዬ በመቆም በንግግር መሃል የአፅንዖት የእጅ ምልከቶችን እንዳደርግ ልከ አንደ አሻንጉሊት አጆቼን ታንቀሳቅስ ነበር ንግግሩ ጉልበት እንዲኖረው የት ማቆም እንዳለብኝ ጭንቅላቴን እንዴት ማንቀሳቀስ አንዳለብኝ እንዲሁም ፍጥነትና ድምፅ እንዴት መጨመር አንዳለብኝ ታስተምረኝ ነበር ፓኪስታን በነበረች ጊዜ የከርከር ቡድን መሪ እንደነበረች ኋላ ላይ ለመገንዘብ ችያለሁ ይህ ደግሞ ከአባዬ ጋር የምታደርገውን ንግግር ለተመለከተ ሰው እውነታነቱ ይገባዋል በዕለተ ኢጅተማ ዕድሜያቸው ከስድስት እስከ ስምንት በሆኑት ሕፃናት ቡድን ውስጥ ነበር የተወዳደርኩት የንግግሩ ርዕስ ደግሞ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ምን ጊዜም እውነትን ብቻ ተናገር የሚል ነበር ላደረኩት ንግግር ሽልማት ተበርከቶልኛል በሌሎች ዘርፎችም የተወሰኑ ሽልማቶችን አግኝቼ ነበርአማና አባይም ተወዳድረው ነበር ነገር ግን የአዋቂዎቹ ውድድር የወጣቶቹን ያህል ሞቅ ያለ አልነበረም ውድድሩ ባጠቃላይ እስልምናን በአዲሱ ትውልድ ዘንድ በማስረፅ ላይ ያተኮረ ይመስላል ወጣት ተሳታፊዎች እንዲካፈሉ በሚል የአዋቂዎቹ ውድድር ከወጣቶቹ በኋላ ነበር የተደረገው ቅድመ ዝግጅ የተደረገበት የማይመስለውን የወንዶቹን የንግግር ውድድር እስከ መጨረሻው ድረስ ለመከታተል ወስፔ ቁጭ አልኩኝ በዚህ ውድድር ላይ የተነሱት ርዕሰ ጉዳዮች ብዙ ነበሩ የአሕመዲ ጀማትን ታሪከ በቅደም ተከል ተናገር ልጆቻችንን በአስልምና መንገድ ለማሳደግ ምን ማድረግ አለብን። በየትኛውም ጥሩ ሙስሊም ሕይወት ውስጥ እአናየዋለን እንዴት እንደምንጸልይ መቸ አንደምንፆም ማንን እንደምናገባ የትኞቹን ምግቦች መብላት አንደሌለብን ይደነግጋል ዋና የሆኑት ጉዳዮች ሁሉ በሸሪኣ ውስጥ ይጠቀለላሉ በቤታችን ውስጥ ከሚገኙት ውድ እቃዎች ዘካት መከፈልን የመሳሰሉ ጥቃቅን ነገሮችንም ጭምር በጥልቀት ይተነትናል ሽማግሌዎቹ በመጠኑ ሳቅ በማለት አጎት ፈይዛን እንዲያጠቃልል ምልክት ሰጡት የሸሪኣን ምንጮችና አተገባበር የተመለከተ አጭር ማብራርያ ይህንን ይመስላል ያኖ ፊሥ አመሰግናለሁፁ ይህንን በማለት ተመልሶ ወለሉ ላይ ተቀመጠ ሽማግሌዎችም ጭንቅላታቸውን በመነቅነቅ አድናቆታቸውን ገለፁ ኋላ ላይ መገንዘብ አንደቻልኩት ቢያንስ ከአሕመዲ ፅይታ አንፃር ለጥያቄው ጥሩ ምላሽ ተሰጥቷል አሕመዲዎች ጥብቅ የሆነ የሥልጣን ተዋረድ ስላላቸው ጠባብ የምርጫ ፅድል ነው ያላቸው የጀማት መሪዎች የሸሪኣን ሕግ ከመተርጎም አኳያ ሙሉ ሥልጣን አላቸው አነዚህ መሪዎች የተናገሩት ነው የሚተገበረው ለአብዛኞቹ ሙስሊሞች ግን እንደርሱ አይደለም ሌሎች ሙስሊሞች ምርጫ አላቸው ለምሳሌ ያህል ሱኒ ሙስሊም ሴት ፍቺ መፈጸም ብትፈልግ ከባለ ሥልጣን ይሁንታ መግኘት ይኖርባታል ይህ ቢያንስ ከሙፍቲ መሆን ይኖርበታል ሙፍቲ በመሠረታዊ የሸሪኣ ሕግ የሰለጠነ ሰው ነው በሙፍቲ ፊት ጉዳይዋን ካቀረበች በኋላፈትዋ የተሰኘ ውሳኔውን ይሰጣታል የእርሱ ፈትዋ ካልተመቻት በሙስሊም ባለሥልጣን የሚደረግ ድንጋጌ ወደ ሌላ ሙፍቲ በመሄድ የተሻለ ፈትዋ መፈለግ ትችላለች ከተለያዩ የአስተሳሰብ ጎራዎች የሆኑ ሙፍቲዎች የተለያዩ አመለካከቶች ስለሚኖራቸው የተለያዩ ፈትዋዎችን ሊሰጡ ይችላሉ ለምሳሌ ያህል አንዳንድ የሱኒ ጎራዎች አንዲት ሴት ለጋብቻ ከመሰጠቷ በፊት ውሳኔዋ መጠየቅ እንዳለበት አፅንዖት ይሰጣሉ ሌሎች ደግሞ ሴት ልጅ በቤተሰቦቿ ውሳኔ ብቻ መመራት እንዳለባት ይደነግጋሉማንም ሰው በየትኛውም የአስተሳሰብ ጎራ የታሰረ ስላልሆነ አንዳንድ ሴቶች በሚመርጡት ፈትዋ ላይ ተመስርተው የአስተሳሰብ ጎራቸውን ይመርጣሉ ይህ ዓይነቱ የፈትዋ ግብይት በሱኒ ሙስሊሞች የማይበረታታ ቢሆንም አሕመዲዎች በጣም ጥብቅ ከሆነው የሥልጣን ተዋረዳቸው የተነሳ ማድረግ ለማይችሏቸው ነገሮች አንደ ጥሩ ምሳሌ ሊጠቀስ ይችላል ውስብስብ ሁኔታውን የሚገልፅ ሌላ ፅንፍም አለሁሉም ቤተ አምነቶች የትኛው ሐዲስ ትከከል ነው በሚለው ጥያቄ ላይ የተለያየ አቋም አላቸው ሐዲሳት ሁለተኛ የሸሪኣ ምንጮች እንደመሆናቸው መጠን እነዚህ የአቋም ልዩነቶች በጉልህ የሚታይ ተፅዕኖ አላቸው ሱኒና ሺኣዎች እስልምናን በተለያዩ መንገዶች እንዲለማመዱ ያደረገው ይህ ጉዳይ ነው የሐዲስ መጻሕፍታቸው አንኳር ልዩነቶች ይታዩባቸዋል እነዚህ ልዩነቶች ኢማሞች ያሏቸውን ሥልጣን በተመለከተ ሺኣዎች ከሚያራምዱት አቋም ጋር ተደምረው ስለ ሸሪኣ ያሉትአመለካከቶች በእጅጉ የተራራቁ እንዲሆኑ አድርገዋል ነገር ግን ዋና ዋና የሆኑት የእስልምና ቤተ እምነቶች የሚግባቡባቸው ነገሮች ከግምት ውስጥ ሲገቡ እነዚህ ልዩነቶች አንሰው ይታያሱ ለምሳሌ ያህል አራቱም ዋና ዋና የሱኒ የአስተሳሰብ ጎራዎችና ሦስቱም ዋና ዋና የሺኣ የአስተሳሰብ ጎራዎች ከአስልምና የሚወጡ ሰዎች መገደል እንዳለባቸው ያስተምራሉ ልዩነቶች የሚታዩት ዝርዝር በሆኑት ለዚያ በሚያበቁ ጉዳዮችና የአፈፃፀም ሂደት ላይ ብቻ ነው ከዚህ ዕድሜ ጠገብ ከሆነው ተግባር ጋር የማይስማሙት ጥግ ላይ ያሉት ለዘብተኛ ሙስሊሞችና አሕመዲያን የመሳሰሉትአናሳ ቡድኖች ብቻ ናቸው እነዚህን ነገሮች የተማርኩት በኢጅተማ ውስጥ አይደለም እዚያ መማርም አያሻኝም በርግጥ አብዛኞቹ ሙስሊሞች ስለ እነዚህ ጉዳዮች ዕውቀት የላቸውም እስልምናን የሚያውቁት በሚለማመዱት ልክ ነው ነገር ግን እነዚህ ጉዳዮች የሊቃውንት ብቻ ናቸው ከምንም በላይ ኢጅተማና ሌሎች መሰል ስብሰባዎችለእስልምና ጥልቅ ፍቅር እንዲኖረንና እርስ በርሳችን የጠበቀ ሕብረት እንዲኖረን አድርገውናል እኛ መልሶቻቸውን ለማናውቃቸው ጥያቄዎች መልስ ያላቸው የሃይማኖት መሪዎች እንዳሉን ማረጋገጫ ሰጥተውናል በየጊዜው በመሰብሰብና ስለ እምነታችን ጉዳዮች በመወያየት ጠንካራ ማሕበረሰብ ሆነናል ምዕራፍ ዘጠኝ የታማኝ ሰው ህልሞች አንድ ምሸት ከተመሳሳይ ስብሰባ በኋላ ከግላስጎው ወደ ዱኑን በመኪናችን እየተጓዝን ሳለን አባና እማ ስለ አንድ ጉዳይ መጨነቃቸው በግልፅ ይታይ ነበር በማርፈዳችን ምከንያት ሆሊ ሎች ላይ ይመላለሱ የነበሩት ጀልባዎች ሥራቸውን ጨርሰው መልህቃቸውን ጥለዋል ቤታችን ለመድረስ ለሁለት ሰዓት ተኩል ያህል የባሕር ሰርጡን መዞር ያስፈልገን ነበር ነገር ግን መሰል ሁኔታዎች ከዚህ ቀደም ቢያጋጥሙንም እማና አባ ሐሳብ ገብቷቸው አያውቅም ነበር ቀጣዩ ቀን እሑድ በመሆኑ ምከንያት አባ ከሥራ ልቀር አችላለሁ የሚል ስጋት ሊገባው አይችልም ሁለቱም ከፊት የተቀመጡ ሲሆን አኛ ልንሰማው በማንቸለው ሁኔታ ዝግ ባለ ድምፅ ይነጋገሩ ነበር ነገር ግን እኔና ባጂ ንግግራቸው ከረር ያለ መሆኑንና የሥጋት ጥላ በመካከላቸው ማጥላቱን ማስተዋል አልከበደንም ነበር የሆነ ችግር ተፈጥሯል ማለት ነው ባጂ አስቀድማ ጠየቀች አባዬ ችግር አለ እንዴ። አባ ጠየቀ ይ የማሊከ ቤት ማረፍ እንቸላለን የሆነውን ይረዱልናል እማ የተናገረችው ነገር ፍርሃቴን ወደ ደስታ ለወጠልኝ የማሊከ ቤተሰቦች ከመስጊድ አባላት ሁሉ የበለጠ የምንቀርባቸው ነበሩ ማሊከና ባለቤቱን ሓአጎቴ እና አከስቴ በማለት ነበር የምጠራቸው ይህ አጠራር በፓኪስታን ባሕል የተለመደ ስለሆነ ብቻ አይደለም ነገር ግን እንደ ሁለተኛ ወላጆቼ ስለምቆጥራቸውም ጭምር ነውባጠፋም ባለማም ሞቅ ባለ ፍቅር ነበር የሚቀበሉኝ አጎቴና አከስቴ ጥሩ ጓደኞቻችን የሆኑ አምስት ልጆች ነበሯቸው የቤተሰቡ ታላቅ ልጅ አስራ ሦስት ዓመቱ ነበር በልጅነቴ እንደ ጥሩ ምሳሌ የምቆጥረው እርሱን ነበር ከእርሱ ጋር የማሳልፈው ጊዜ እጅግ አስደሳች ነበር ለጊዜውም ቢሆን ያልተለመደው የጎዞ መስተጓጎል ተረስቷል ይህንን ያልታሰበ መስተጓጎል የበለጠ አጓጊ የሚያደርገው ደግሞ በጓደኛቼ ቤት ውስጥ ለመጀመርያ ጊዜ ማደሬ ነው ቤተሰቦቻችንን ለመጎብኘት ወይም በሌላ ምከንያት ጉዞ ላይ ካልሆንን በስተቀር ከቤት ውጪ አድረን አናውቅም አብሮን የሚያድር ጓደኛ ባለመኖሩ ምከንያት ብቻ ሳይሆን አማ ከእርሷ ዕይታ መራቃችን ስለማያስደስታት ከቤተሰብ ተነጥሎ መተኛት የማይታሰብ ነው የገበታ ጫወታዎችን እየተጫወትንና ፊልም እያየን ሌሊቱን አጋመስን ወላጆቻችን ከተኙ በኋላ ጓደኞቼ ሬዴሂየተሰኘ ርዕስ ያለው አስፈሪ ፊልም በቪድዮ ማጫወቻው ውስጥ ጨመሩ የቤተሰብ ቁጥጥር ተለይቶኝ ስለማያውቅ እንደዚያ ዓይነት ፊልም አይቼ አላውቅም ነበር ፊልሙ ከጀመረ ከአፍታ በኋላ ከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ ገባሁ የጓደኞቼ ማባበል እንኳ ቴሌቪዥኑን እንዳይ አላደረገኝም ወደ መኝታዬ በመሄድ ለመተኛት ሞከርኩኝ በዚያን ሌሊት የሰዎች አደን የደም ነጠብጣቦችና አስፈሪ የሆኑየኦስትሪያውያን ቅላፄዎች በህልሜ እየተፈራረቁስቃዥ ጎህ ቀደደ ወደ መኝታ ከሄድኩበት ጊዜ ይልቅ አካሌ ዝሎ ከአልጋ ላይ ወረድኩ በበነጋው ለንጉሣዊ ቤተሰብ የተዘጋጀ የሚመስለውን የፓኪስታንና የስኮትላንድ ምግቦች ድብልቅ የሆነውን ቁርስ ከበላን በኋላ እማ አከስቴን አመስግና ወደ በሩ ተጠግታ በመቆም ከአጎቴ ጋር ሲያወጋ የነበረውን አባን መጠበቅ ጀመረች እማ በቂ እንቅልፍ አለመተኛቴን ስላወቀች ሁሌም ሲደከመኝ እንደማደርገው እርሷን ደገፍ ብዬ መቆሜን አልተቃወመችቸም አክስቴ መንገዱን እየተመለከተች መናገር ጀመረች አሁን ቀን ስለሆነ ያየውን ልትነግሪኝ ትቸችያለሽ በቀን እንኳ ለሰው የማትናገሪው ዓይነት ህልም እኮ ነው የእንቆቅልሹ መልስ ይህ ነበር አባ ህልም አልሟል በኛ ባሕል ህልም እንደ ዋዛ አይታይም አንድ ተኣማኒ ሐዲስ እንደሚናገረው የታማኝ ሰው ህልም ትንቢታዊ ነው እኔ እስከማውቀው ድረስ አብዛኞቹ ሙስሊሞች በቀጥታ ከፈጣሪያቸው ዘንድ መልእከት የሚጠብቁት በህልም በኩል ብቻ ነው ለዚህ ደግሞ ጥሩ ምከንያት አለህልሞች ብዙ ጊዜ ይፈፀማሉ አባ ብዙ ትንቢታዊ ህልሞችን አይቷል እንደ ምሳሌ ለመጥቀስ ያህል የሆነ ወቅት ላይ ለማዕረግ ዕድገት የውድድር ፈተና ወስዶ ነበር በፈተናው ዕለት እርሱና አምስት ጓደኞቹ ከባድ ተኩስ በበዛበት የጦር ሜዳ ውስጥ ሲዋጉ ህልም አየ ከአደጋ ለማምለጥ አንድ በርቀት የሚታይ አጥር መዝለል ነበረባቸው ስድስቱም መሮጥ ጀመሩ አባ መጀመርያ አጥሩን ዘለለ እርሱን ተከትሎ ደግሞ ሌላው ጓደኛው ዘለለ የተቀሩት አራቱ መዝለል አልቻሉም ከጥቂት ሳምንታት በኋላ የፈተና ውጤት ሲመጣ በህልሙ ያያቸው አምስቱም ጓደኞቹ ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ማለፍ የቻሉት ግን ልከ በህልሙ እንዳየው እርሱና አንዱ ጓደኛው ብቻ ነበሩ ትልቋ እማ አንድ ጊዜ አባቷ ከሞተና ከተቀበረ ከቀናት በኋላ ህልም አልማ ነበር ሙሉ በሙሉ በዝናብ በስብሶ በር ላይ በመቆም እያንኳኳ አርዳታዋን ይጠይቅ ነበር ለሦስት ተከታታይ ቀናት ተመሳሳይ ህልም ካለመች በኋላ ሰደቃ ብዙ ጊዜ ከፉ መቃብሩን ሄዳ ለማየት ወሰነች አዚያ ስትደርስ አውሬ አጋጣሚዎችን ለማስወገድ ጉድኋዱን ቆፍሮት ጎርፍ ገብቶበት ተመለከተች የሚሰጥ በበጎ ፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ስጦታ የቦተሰቤ አባላት ስለ ህመም የፅንስ መጨንገፍ ልደት አልሀምዱሊላህ ምስጋና ሞትና ስለ ብዙ ጉዳዮች ቀጥተኛ ህልሞችን አልመዋል ሁሉ ለአላህ ይሁን ህልም በተለይ ሊታለፍ የሚችልን አደጋን የሚያስጠነቀቅ የሚል ትርጉም ያለው ከሆነ እንደዋዛ አናየውም የሙስሊሞች የተለመደ አባባል ኔሐዖፖ ከሚለው ጋር የሚመሳሰል አስላማዊ የምስጋና ቃል ነው አከስቴ እማ ህልሙን ለሆነ ሰው መንገር እንደሚያስፈልጋት ስለተገነዘበች ደግማ ጠየቀቻት ሰደቃ በመስጠት ልጸልይላችሁ ስለምፈልግ ያየውን ንገሪኝ እማ ትንሽ አቅማማች እሺ እነግርሻለሁ ነገር ግን ትርጉሙ ምን አንደሆነ አላውቅም ለሌላ ሰው ደግሞ መንገር የለብሽም ህልሙን ያየው ከሁለት ቀናት በፊት ነበር ሁላችንም መኪናችን ውስጥ ሆነን በጨለማ መንገድ ላይ እናሽከረከር ነበር መንገዱ ጠባብ ሲሆን ከዳርና ዳር እሳት ነበር አሳቱ ራሱ ጨለማዊ ሲሆን ምንም ብርሃን አልነበረውም ምንም ነገር አይታየውም ነበር ባጂና ነቢልን ዞር ብሎ ሲያያቸው ጠፍተዋል እማ ንግግሯን በመግታት መኪናው አጠገብ ቆመው የነበሩትን አባንና አጎቴን በዝምታ ተመለከተቻቸው አክስቴ ትርጉሙ ምን ይመስልሻል። ብዙ ትርጉም ሊኖረው ይቸላል አንድ ሰው ምን አንደሚወድና ምን እንደሚያምን ለማወቅ ከፈለጋችሁ በግል መጠየቅ በእጅጉ አስፈላጊ ነው ነገር ግን አንድን ሰው ቀርበን ከማወቃችን በፊት ልናደርገው የምንችለው ትልቁ ነገር ቢኖር ስደተኛ ወይንም ሁለተኛ ትውልድ ሙስሊም መሆን አለመሆኑን ማጣራት ነው ይህ አንዱ ሁኔታ ብዙ ጊዜ ትልቅ ልዩነት ይፈጥራል ምዕራፍ አሥራ ሦስት ራስን መሳት እና መተካካት ምስራቃዊ ሰው እንደ መሆኔ መጠን ከምዕራባውያን ጋር የነበረኝ ተግባቦት የተቃኘው በእስላማዊ ዓቀበተ እምነት ነበር የኔን ትውልድ እስረኛ ካደረገው የድህረ ሥልጣኔ አንፅሮት ጋር ትግል ማድረግ እምብዛም አላስፈለገኝም ነበር በኔ አመለካከት አውነት ፍንትው ብላ የምትታይ ናት አውነት ከሌለች እውነት የለችም የሚለው አባባል ራሱ እውነት ይሆንና ለእውነት መኖር ምስከር ይሆናል ምርጫ የለም እውነት መኖሯ ግድ ነውበተለምዶ ሙስሊሞችና ከርስቲያኖች ይህንን አስተሳሰብ ይጋሩታል ሁለቱም በእውነት መኖር ያምናሉ ቢያንስ ሃይማኖታቸው እውነት መሆኑን ያምናሉ ነገር ግን የጋራ አስተሳሰቦቻቸው ከዚህ የላቀ ነው አሃዳዊነትን መንፈሳዊና ቁሳዊ አፅናፋትን መላእከትንና አጋንንትን መልካምና ከፉን የመጨረሻውን ፍርድ ገነትና ገሃነምን የቅዱሳት መጻሕፍትን ግልጠተመለኮት አንዲሁም ሴሎች ጥቃቅን አሳቤዎችን በተመለከተ በግርድፉ ተመሳሳይ የሆነ እምነት ነው ያላቸው እነዚህ የጋራ ጉዳዮች በሁለት ወገን እንደተሳለ ሰይፍ ናቸው ሁለቱም ዓለምን ከተመሳሳይ የዕይታ ፅንፍ አንዲመለከቱ በማድረግ ለውይይትና ለመግባባት የጋራ መደላድልን ይፈጥራሉ ነገር ግን አነዚህ የጋራ ነገሮች በሃይማኖታቱ ቁልፍ አስተምህሮዎች ላይ ያሉትን ልዩነቶች ማከረር ይችላሉ ለምሳሌ ያህል እስልምናና ክርስትና ስለ ኢየሱስና ስለ መሐመድ ያላቸውን ልዩነቶች ማየት ይቻላል በክርስቲያኖች እምነት መሠረት ኢየሱስ የተሠገወ አምላከ ነው ይህ እምነት ደግሞ ለታሪካዊው ከርስትና እጅግ ቁልፍ ነው ሙስሊሞች ኢየሱስ ከነቢይ በላይ እንዳልሆነ ያምናሉ የተሠገወ አምላከ አድርጎ እርሱን መቁጠር በቁርአን መሠረት ከህደት ሲሆን ወደ ገሃነም ያወርዳል በሙስሊሞች አምነት መሠረት መሐመድ የአላህ መልእክተኛ ነው ይህ አምነት ወሳኝ ከመሆኑ የተነሳ የሸሃዳ ግማሽ ከፍል ነው በከርስቲያኖች አምነት መሠረት በኢየሱስ በኩል የሚገኘውን መዳን የሚያበስረውን ወንጌል የሚፃረር ትምህርት የሚያስተምሩ ሰዎች ሀሰተኛ መምህራን ናቸው በሙስሊሞችና በክርስቲያኖች መካከል የሚደረጉት ውይይቶች በኢየሱስና በመሐመድ ላይ የማተኮራቸው ምከንያት ይህ ልዩነት ነው ሙስሊም ወጣት እንደመሆኔ መጣን የእስልምና ውጤታማ አምባሳደር ለመሆን ጥሩ ተቀባይነት ከማግኘት በዘለለ በነዚህ ልዩነተች ላይ ጥልቅ ዕውቀት ሊኖረኝ እንደሚያስፈልግ አስብ ነበርመሐመድን በተመለከተ ምዕራባውያን ያላቸው ፅውቀት በእጅጉ አናሳ ነው ስለ አርሱ የፈለኩትን ነገር ብናገር ሰዎች ያምኑኛል ማንንም የማታለል ፍላጎት ባይኖረኝም ነገር ግን አብዛኞቹ ከርስቲያኖች ዕውቀት ስለሌላቸው ስለ መሐመድ ጥሩ ጥሩ ነገሮችን በመናገር ማሳመን ቀላል ነው በልጅነቴ የተማርኳቸውን ነገሮች በተለይም ወደ መካ በተመለሰ ጊዜ ያሳየውን ደግነት በመናገር ሰዎች ለመሐመድና ለእስልምና ያላቸው አመለካከት ከቀድሞው የተሻለ እንዲሆን ያደረኩባቸው ጊዜያት ነበሩ ኢየሱስን በተመለከተ ሙስሊሞች ከከርስቲያኖች ጋር የማይስማሙባቸው ሁለት ቁልፍ ጉዳዮች አሉ እነርሱም ኢየሱስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ መሞቱና አምላከነቱን መናገሩ ናቸው ቁርአን እነዚህን ሁለቱን እምነቶች ያስተባብላል ጥሩ የአስልምና አምባሳደር ለመሆን እነዚህን ሁለቱን ጉዳዮች በጥልቀት ማጥናትና ኢየሱስ አምላከ መሆኑን አለመናገሩን እንዲሁም በመስቀል ላይ አለመሞቱን ሽንጤን ገትሬ መሟገት ያስፈልገኛል ሁለተኛውን በተመለከተ የኛ ቤተ አምነት መስራች ጀማቱን ለማስታጠቅ አነስተኛ ከታብ ጽፏል ፈይፉዕ ዕሓድ ጸየሚል ርዕስ ያላት ስትሆን ብዙ ጊዜ ደጋግሜ አንብቤያታለሁ የተማርኩትን በመያዝ ለመጀመርያ ጊዜ የተሟገትኩት በትምህርት ቤታችን በር ፊት ለፊት አውቶብስ ውስጥ ሆነን ወደ ቤት ለመሄድ ዝግጅት ላይ በነበርንበት ጊዜ ነበር የፋሲካን መቃረብ ምክንያት በማድረግ ትምህርት ሲዘጋ ምን ለመሥራት እንዳቀድኩኝ ከጓደኛዬ ከከሪስተን ጋር እያወጋሁ ነበር ግፍያ ሳይበዛ ከከፍላችን ቀደም ብለን በመውጣት መኪናው ላይ ተሳፈርን በዕድሜ ከፍ ያልን ስለነበርን የኋላውን ወንበር ነበር የያዝነውአርብ የስቅለት ፅለት ምን ለማድረግ እንዳቀደች ከፊት ለፊቴ ተቀምጣ ትነግረኝ ጀመር ድ ፍሪዴይ መልካሚቱ አርብ ስትዬ ምን ለማለት ፈልገሽ ነው። የሚል ጥያቄ መነሳቱ የማይቀር ነው የተለያዩ ሰዎች ይጠቀሳሉ አንዳንዶች በኢየሱስ ፋንታ የመሞትን ከብር መውሰድ የፈለገ አንድ ወጣት ሰው መሆኑን ተናግረዋል ሌሎች ደግሞ የኢየሱስን መስቀል የተሸከመው የቀሬናው ስምዖን ተሰቅሏል ይላሉ አላህ ፍትሃዊ ፍርድ ለመፈፀም ሲል የኢየሱስን መልከ ለአስቆሮቱ ይሁዳ ሰጠው የሚሉም አሉ በዚህ ዘመን ይህ የመጨረሻው መላ ምት በሙስሊሞች ዘንድ የበለጠ ተቀባይነት ያለው ይመስላል የኢየሱስ እርገት በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት አለው ቁርአን አላህ ኢየሱስን ወደ ራሱ አነሳው ይላል ይህ ደግሞ ሙስሊሞች የኢየሱስን እርገትና ምፅዓት እንዲያምኑ ምከያት ሆኗቸዋልሹ ስለዚህ እንደ ከርስቲያኖች ሁሉ አብዛኞቹ ሙስሊሞች የመሲሁን ዳግም ምፅዓት ይጠባበቃሉ አሕመድ መሲሁ መሆኑን በመናገሩ ምከያት የኛ ጀማት ይህንን አመለካከት አይቀበልም መጽሐፍ ቅዱስን በመጥቀስ አይሁድ የኤልያስን ከሰማይ መምጣት መጠበቃቸው ስህተት ነው ብሏል ኢየሱስ መጥምቁ ዮሐንስምፅዓተ ኤልያስ መሆኑን ተናግሯል በተመሳሳይ መንገድ ዓለም የኢየሱስን መምጣት ቢጠብቅም እርሱ ግን በሚርዛ ጉለም አሕመድ በኩል ተመልሷልበእርግጥ የኛ ጀማት የሚያስተምረውን ሁሉ ዓይኔን ሳላሽ ስለምቀበል ኢየሱስ አርጓል ከሚለው አመለካት ይልቅ ወደ ሕንድ በመሄድ እዚያ ሞቷል የሚለውን አመለካከት በመደገፍ ነበር እከራከር የነበረው አመለካከቴን ለሌሎች ባካፈልኩኝ ቁጥር አምነቴ እየጠነከረ ይመጣ ነበር ሰዎች የኔን አመለካከት ውድቅ ለማድረግ የሚያስቸል ምንም የረባ ነገር አለማቅረባቸውን ስመለከት ደግሞ የበለጠ ድፍረት በማግኘት እሰብክ ጀመር የእስልምና አምባሳደር ለመሆን የሚያበቃኝን ግማሹን የከርከር ርዕስ በጥልቀት ያወቅሁት ሆኖ ተሰማኝ የተቀረው ደግሞ ከዚያ እንደሚቀል አሰብኩኝ ልከ ነበርኩኝ ምዕራፍ አሥራ አራት አብ ከኢየሱስ ይበልጣል አሥረኛ ከፍል ስደርስ የግል ሕይወቴ ጉልህ በሆነ ሁኔታ መለወጥ ጀመረ ከጓደኞቼ ጋር በስልከ በመነጋገርም ሆነ በትምህርት ቤት ረዘም ያሉ ጊዜያትን የማሳለፍ ነፃነት ነበረኝ ልብሶቼን እናቴ የምትመርጥልኝ ሲሆን ለአለባበስ እጨነቅ ነበር ቀለሜዋ ላለመምሰል የንባብ መነፅር ከማድረግ ይልቅ በዓይን ብሌን ላይ የሚለጠፍ ሌንስ እንዳደርግ አንዲፈቀድልኝ እናቴን ብጠይቃትም ፍቃደኛ አልሆነችም የምዕራባውያን ባሕል ተፅዕኖ ልቋቋመው የምችለው ዓይነት አልነበረም አሁንም ድረስ ውጪ እንዳድርና የትምህርት ቤት የጭፈራ ዝግጅቶች ላይ አንድታደም አይፈቀድልኝም ነበር ከጓደኞቼ ጋር የነበረኝ ቅርርብ ስለበረታ ከእነዚህ ዝግጅቶች መቅረት አስቸጋሪ ነበር አንድ ቀን በላቲን ቋንቋ ከፍለ ጊዜ እንደሆነው አምነቴ በቀጥታ በሚጠቀስበት ወቅት በኩራት እስልምናን ለመወከል መቆሜን አላስተጓጎልኩም በፕሪንሰስ ኣን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላቲን የሚያስተምሩ ሁለት መምህራን ነበሩ ተማሪዎቻቸው በትምህርቱ ደስተኛ መሆናቸውን ሲገልፁ እነዚህ መምህራን በደስታ ይፈነድቁ ነበር ላቲን ሁለትን ታስተምር የነበረችዋ መምህርት ኢርለስ ከሚገባው በላይ ትቀርበኝና ደግነትን ታሳየኝ ነበር የላቲን ቋንቋንና የእርሷን ከፍለ ጊዜ በጣም ነበር የምወደው የሚገስፀኝ ሰው ባለመኖሩ የተነሳ ከጊዜ ወደ ጊዜ ፀባዬ ተለውጦ ተንኮለኛ መሆን የጀመርኩበት ወቅት ነበር የቤት ሥራዬን ብዙ ጊዜ የምረሳ ዓይነት ተማሪ ስለሆንኩ ወደ ከፍል ከመግባቴ ከጥቂት ሰዓታት በፊት በማስታወስ በጥድፊያ ሞነጫጭሬ ለመጨረስ እሞከር ነበር የመምህርት ኢርለስ ከፍለ ጊዜ ከእስፓኒሽ በፊት ስለነበረ ብዙ ጊዜ እርሷ ስታስተምር ከፍል ውስጥ ሆፔ የእስፓኒሽ የቤት ሥራ እሠራ ነበር የእስፓኒሽ መጽሐፌን ከላቲን ስር በመደበቅ እርሷ ለመጻፍ ወደ ጥቁር ሰሌዳው ስትዞር አየፈፀምኩ ያለሁትን ነገር እንደማታውቅ በማሰብ የቤት ሥራዬን አሠራ ነበር በዓመቱ አጋማሽ ላይ ግን የማደርገውን እያወቀች መጥፎ አመሌን መታገሷን ተረዳሁኝ ከዕለታት በአንዱ ቀን የእስፓኒሽ የቤት ሥራዬን አየሠራሁ ሳለሁኝ አንዲት ልጅ ወደ እኔ በመዞር ኀቢል የሆነ ነገር ልጠይቅህ ፈልጌ ነበር አለችኝ ስሟ ቤስቲ ይሰኛል በክፍላችን የምትገኝ የተመሰከረላት ከርስቲያን ነበረች ሁሉም ሰው የወንጌላዊት ቤተ ከርስቲያን አባል መሆኗን ያውቃል ብዙ ጊዜም ስለ እምነቷ ጥብቅና ትቆም ነበር ከደግነቷና ሌሎችን ከመርዳት ፍላጎቷ ባሻገር ለስለስ ያለ ነገር ግን ሁላቸንንም የሚስፈራ አቀራረብ ነበራት ችግር እንዳለባት እናስብ ነበር ይቻላል አልኳት ምን ልትለኝ እንደሆነ ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም አርሳስ ፈልጋ ቢሆን ኖሮ በቀጥታ ትነግረኝ ነበር እንጂ የሆነ ነገር ልትጠይቀኝ አንደፈለገች መናገር አያስፈልጋትም ነበር እኔ ደግሞ ሁል ጊዜ አርሳሴን ረስቼ እንደምመጣ ስለሚታወቅ እኔን መምረጥ አልነበረባትም ትንሽ ፀጥ ብላ ከቆየች በኋላ ስለ ኢየሱስ ታውቃለህ። ቤስቲ መረጃ የያዘ ካርድ በፈገግታ አቀበለችኝ ከፈገግታዋ በስተጀርባ ከዚህ ቀደም ያላየሁትን ነገር አስተዋልኩኝ ደንግጣለች የፈገግታዋን አፀፋ መለስኩላት ምዕራፍ አሥራ አምስት የሰማይ ደጆችና የገሃነም ነበልባሎች ወደ ቤተ ከርስቲያን በመጋበዜ በጣም ደስ ብሎኛል ከዚያ ቀደም አንድ ቀን ወደ ካቶሊክ ቤተ ከርስቲያን መሄዴን አስታውሳለሁ በላቲን የሚደረገው ቅዳሴ ለጆሮ ይጥማል እውነቱን ለመናገር ለምን እንደተጋበዝኩኝ ግራ ገብቶኝ ነበር ቤንና ቤተሰቡን ጨምሮ ካቶሊክ ያልነበሩ የተወሰኑ ጓደኞቼም በቦታው መገኘታቸውን አስታውሳለሁ በመደዳ ቆመን እያለን ሰዎች ከቄሱ እጅ የሆነ ነገር ለመቀበል ወደ ፊት ሲሄዱ ተመለከትኩኝ ምን ማድረግ አንዳለብኝ ስለማላውቅ አብሬያቸው ወደ ፊት ለመሄድ ተነሳሁ የቤን እናት እጄን በመጎተት ወንበር ላይ አስቀመጠችኝ ግራ ገብቶኝ ተመለከትኳት ጭንቅላቷን በማወዛወዝ በፍፁም መሄድ እንደሌለብኝ ምልከት አሳየችኝ እስከዚያች ደቂቃ ድረስ ፊቱን ቅጭም አድርጎ የነበረው ካህን ሳቅ አፍኖት ተመለከትኩኝ የፕሮቴስታንት ቤተ ከርስቲያን የተለየ መሆኑን ማንም ስላልነገረኝ ተመሳሳይ ነገር እንደሚኖር እጠብቅ ነበር የኖርፎልከ ባፕቲስት ቤተ ከርስቲያን ሕንፃ አዳራሸ መስሎ ታየኝ የቤተ ከርስቲያን ሥርኣት የሚፈፀመው ሌላ ሕንፃ ውስጥ ሊሆን እንደሚቸል በማሰብ ዙሪያ ገባውን ብማትር ምንም የሚታይ ነገር አልነበረም ወደ መጨረሻ ጥግ ላይ ከአባቴ ጎን ነበር የተቀመጥኩት ጫወታው ምን እንደሆነ ባናውቅም ግብዣውን በመቀበሌ አባቴ ደስተኛ ነበር አለመቀበል ነውር መሆኑንና ከቤስቲ ጋር ውይይት ለመቀጠል ጥሩ በር እንደሆነ ተናግሮ ነበር እምነቴን ለማካፈል በመቻሌ ኩራት ተሰምቶት ነበር በዚህ ቦታ የሚታየውን ድራማ መረዳት እንድችል ሊያግዘኝ ነበር አመጣጡ የትዕይንቱ ርዕስ የሰማይ ደጆችና የገሃነም ነበልባሎች ይላል የከርስትናን የደህንነት እሳቤ የሚገልፅ ነው ከርስቲያኖች ይህንን መልዕከት ወንጌል በማለት እንደሚጠሩት ለመጀመርያ ጊዜ የሰማሁት በዚህ ድራማ ነበር ወንጌል የሚለው ቃል ስለ ኢየሱስ የሚናገሩትን አራቱን የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ብቻ አእንደሚያመለክከት ነበር የማውቀው ድራማው በቀጠለ ቁጥር መልዕከቱ እየጎላ ይሄድ ነበር ኢየሱስን እንደ ጌታ ከተቀበላችሁ ወደ ሰማይ ትሄዳላችሁ አለበለዝያ ወደ ገሃነም ትወርዳላችሁ ይላል እያንዳንዱ ከፍል የሚጠናቀቀው አንድ ሰው ወደ ሰማይ ወይም ወደ ገሃነም ሲሄድ በማሳየት ነበር ይህ ደግሞ ኢየሱስን በመቀበል አለመቀበላቸው ላይ የተመሠረተ ነው የድራማው ምስል ጥርት ያለ አልነበረም አንድ ሰው ወደ ሲዖል ሲወርድ ቀይና ቢጫ ቀለማት በከፍሉ ውስጥ ይበራሉ ነጎድጓዳማ ድምፆች በማይከራፎን ያስተጋባሉ ሰይጣንም በመምጣት ኃጢኣተኛውን ሰው እያሽካካ ከመድረክ ላይ ጎትቶ ይወስደዋል አንድ ሰው ኢየሱስን ከተቀበለ ደግሞ የሚያንፀባርቁ መላአከት በመምጣት ብርሃናማ ወደ ሆነ በር በደስታ ይመሩታል በትዕይንቱ መጠናቀቂያ ላይ አንድ ሰው መኪና እየነዳ ተሳፋሪው ስለ ኢየሱስ ሲነግረው ይታያል ሰውየው ብዙ መጥፎ ነገሮችን እንደሠራና በዘመኑ ሁሉ ከእግዚአብሔር ርቆ እንደኖረ ይናገራል ተሳፋሪውም ኃጢኣተኛ መሆኑንና ኢየሱስ እንደሚያስፈልገው ካሳመነው በኋላ የንስሐ ጸሎት አስጸለየው ጸሎቱን ገና ከመጨረሱ አሳቃቂ አደጋ ደረሰ መብራቱ ጭልምልም በማለቱ ሁለቱም ሰዎች መሞታቸው ታወቁቀ መብራት ተመልሶ ሲበራ ደስ የሚል የሙዚቃ ድምፅ እየተሰማ ሾፌሩ ወደ ሰማይ ተወሰደ ሆነ ተብሎ ታስቦ እንደሆን ባላውቅም ነገር ግን ሁላችንም ወደየ ቤቶቻችን ለመሄድ መኪናችን ውስጥ ከመግባታችን በፊት ድራማው በዚያ መልኩ ማለቁ ግሩም ሐሳብ ነበር እኔና አባቴ መኪናችን ውስጥ ገብተን ቀበቷችንን አጥብቀን ጉዞ እንደጀመርን አባዬ የውይይት ጥያቄ አቀረበ ነቢል ስለ ድራማው ምን ታስባለህ። የሚል ነበር ውይይቱ ጥልቅና በአምላከ መኖር የሚያምኑ የብዙ ተማሪዎችን እምነት ያናወጠ ነበር ውይይቱ ያተኮረው በቋሚ ሙግቶች ላይ ቢሆንም ግላዊ ዕውቀቶች የበለጠ ኃይል እንዳላቸው ተገንዝቤያለሁ ቀለማቱን በሰማይ ውስጥ ማየቴንና ወደ ጓደኞቼ እንደመሩኝ ብናገር ማንም እንደማይቀበለኝ አውቃለሁ ያንን ማድረግ ደግሞ አስፈላጊ አልነበረም ምልከቱ ለግሌ የተሰጠ እንጂ ለሌላ ሰው አይደለም አምላከ መኖሩን ከመቶ ከማመን መቶ በመቶ ወደ ማመን አምጥቶኛል ከአራት ዓመታት በኋላ የኔ ዓለም መፈራረስ ሲጀምር ያቺ አንድ ከመቶ የጎላ ሚና መጫወት ችላለኾ ምዕራፍ አሥራ ስምንት ከክብርና ሥልጣን ቲኦኬ ከምርጥ ጓደኛዬ ከዴቪድ ጋር ከተማርኳቸው ትምህርቶች መካከል አንዱ ነበር ቅርርባችን እያደገ ሄዶ የትምህርት ደረጃቸን ሲጨምር መለያየት እስከማንችል ድረስ ደርሰናል ከሰባቱ ትምህርቶቻቸን መካከል ስድስቱን በጋራ የምንማር ሲሆን የጎበዝ ተማሪዎች ቡድን መሪዎች ሆነን የምርምር ቡድን ተቀላቅለን ነበር ዴቪድና እኔ የመጀመርያ ዓመት ተማሪዎች ውድድርን ከአኛ ግዛት በአምስተኛነት ደረጃ በማጠናቀቅ ከፍተኛ አድናቆት አትርፈን ነበር ሁለታችንም ገና ጀማሪዎች አንደመሆናችን መጠን ያንን ደረጃ ማግኘት የማይታሰብ ነበር ሁለተኛ ዓመት ስንሆን ደግሞ ከግዛቱ አንደኛ በመውጣት ተሸልመናል ዴቪድና እኔ ስለ ሃይማኖትና ስለ እግዚአብሔር መኖር የምንወያየው አልፎ አልፎ ብቻ ነበር ብዙ ጊዜ የማይገጥሙ አመለካከቶችን የምናራምድ ሲሆን አስተዳደጋችን ተፅዕኖ አሳድሮብናል እርሱ የፈጣሪን መኖር በጥርጣሬ ነበር የሚያየው እኔ ደግሞ እንደ ሙስሊም ነው የማስበው በቲኦኬ ከፍለ ጊዜ የነበረው ውይይት የእርሱን ጥርጣሬ ከፍ ያደረገ ሲሆን የኔን እምነት ግን ቅንጣት ታከል አልቀነሰም ነበር ቤተሰቦቼ እምነቴን እንድመረምር ሲነግሩኝ ያስተማሩኝን ነገሮች እንዴት አድርጌ ከጥቃት መከላከል እንደምችል እንዳስብ ነበር ከእኔ የሚጠብቁት በቲኦኬ ከፍለ ጊዜም ተመሳሳይ ነገር ነው የምንማረው ማለትም አምነታችንን አንድንመረምር ነው የምንማረው ነገር ግን በተግባር ፍፁም የዚያ ተቃራኒ ነው አምነታችንን በጥልቀት በመመርመር አእንገዳደረዋለን ደካማ ጎኑን እናያለን ከዘመኑ ጋር መሄድ አለመሄዱን እንፈትሻለን አንዳንድ ተማሪዎች እንዲያውም አምነታቸውን እስከመለወጥ ደርሰዋል ይህ በምዕራብና በምስራቅ መካከል የሚገኝ ልዩነት ሙስሊም ስደተኞችን ከልጆቻቸው ከሚለዩ ነገሮች መካከል አንዱ ነው አስላማዊው ባሕል ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያሉትን ሰዎች ሥልጣን የሚያጎናፅፍ ሲሆን በምዕራብ ባሕል ደግሞ ባለ ሥልጣኑ ምክንያታዊነት ነው እነዚህ ሁለቱ የሥልጣን ባለቤቶች የአጠቃላዩን ማሕበረሰብ የሥነ ምግባር መለኪያ የሚወስኑ ናቸው ሥልጣን ከምክንያታዊነት ይልቅ በሰዎች ደረጃ ላይ የተመሠረተ ከሆነ የሰዎችን የመሪነት ሚና መግጣዳደር አደጋ ያስከትላል ምከንያቱም ሥርኣቱን የማስቆጣት ሁኔታ ይኖረዋልና አመፅ ቅጣትን ያስከትላል መታዘዝ ደግሞ ሽልማትን ያስገኛል ትከከለኛ የሆኑና ያልሆኑ ተግባራት በግል ደረጃ ሳይሆን በማሕበረሰብ ደረጃ ነው የሚወሰኑት የአንድ ሰው ስብዕና የሚወሰነው ማሕበረሰቡ ከእርሱ የሚጠብቀውን በማሟላት አለማሟቱ እንጂ በግል ትከከልና ትከከል ያልሆነውን ለይቶ በመፈፀሙ አይደለም ከዚህ የተነሳ በየበላይነት ላይ የተመሠረተ ሥልጣን ትከከልና ስህተትን በከብርና በውርደት ላይ ተመስርቶ የሚወስን ማሕበረሰብ ያፈራል በሌላ ወገን ደግሞ ሥልጣን በምከንያታዊነት ላይ የተመሠረተ ከሆነ ጥያቄዎች የሥልጣንን መሠረት ስለሚያጠናከሩ በደስታ ይስተናገዳሉ እያንዳንዱ ሰው የራሱን ተግባር በጥልቀት እንዲያጤን ይጠበቅበታል ትከከል የሆኑና ያልሆኑ ተግባራት በግል ይመዘናሉ የአንድ ሰው ስብዕና የሚወሰነው ሰውየው ትከከል እንደሆነ የሚያውቀውን ነገር በማድረግ አለማድረጉ ነው ምክንታዊ የሆነ ሥልጣን ትከክልና ትክከል ያልሆነውን ነገር በንፅህናና በጥፋተኝነት ላይ ይመሰርታል ምዕራባውያን ምስራቃውያንን የማይረዱበት ትልቁ ምከንያት በንፅህናና በጥፋተኝነት ላይ በተመሠረተው በራሳቸው ንፅረተ ዓለም መነዕር በከብርና በውርደት ላይ የተመሠረተውን የምስራቁን ንፅረተ ዓለም ለማየት መሞከራቸው ነው በእርግጥ ይህ ጉዳይ እጅግ ውስብስብ ነው የሁለቱም አመለካከቶች ቅንጣቶች በምዕራቡም በምስራቁም አንፅሮታት ውስጥ የሚገኙ ቢሆኑም ከብርና ውርደት ግን የምስራቁን አመለካከት የሚቃኝ ማዕከላዊ ጉዳይ ነው ምዕራባውያን ደግሞ ይህንን ለመረዳት በእጅጉ ይቸገራሉ ለብዙ ምዕራባውያን አስደንጋጭ የሆኑት በብዙ ሙስሊም አገራት የሚታዩት እንደ ከብር ግድያዎች የስድስት ዓመትና ከዚያ የሚያንሱ ህፃናትን መዳር እና ደም መፋሰስ የዚያ ውጤቶች ናቸው በነዚህ አገራት የሚገኘው መሕበረሰባዊ አደረጃጀት እነዚህን ተግባራት ተቀባይነት እንዲኖራቸው ከማድረግ አልፎ ተመራጭ ያደርጋቸዋል ምንም ያህል ምከንያታዊነትም ሆነ የውጪ ተፅዕኖ አነዚህን ልማዶች ሲያስወግድ አይትልም ለውጡ ከውስጥ የሚመነጭ ማሕበራዊና አገር በቀል ሊሆን ይገባዋል ነገር ግን ከላይ የተዘረዘሩት ቸግሮች በምዕራብ ለሚወለዱት ሁለተኛ ትውልድ ሙስሊሞች በደምሳሳው ችግር የሚፈጥሩ አይደሉም እጅ ከፍንጅ ካልተያዛችሁ ችግር የለውም ከሚለው የከብርና የውርደት መርህ ጋር ነው የምንታገለው ውርደት የማያስከትል ከሆነ ችግር የለውም ይህ መርህ ዕድሜዬ በጨመረ ቁጥር በጥሩ ሁኔታ ሲሰራ አስተውያለሁ እኔና ብዙ ሙስሊም ጓደኞቼ ከሰዎች ፅይታ ተሰውረን ብዙ ጥሩ ያልሆኑ ነገሮችን እንፈፅም ነበር ለምሳሌ ያህል የሚጠጣ ውጎ ከገዛን በኋላ አጭበርብረን ሶዳ እናስጨምር ነበር ነገር ግን አንድ ቀን በቨርጂንያ በሚገኘው ታኮ ባሕር ዳርቻ ሳለን ከጓደኞቼ መካከል አንዱ ተመሳሳይ ነገር ሲፈፅም አስተናጋጁ እጅ ከፍንጅ ያዘው ውኀ ነው ያዘዝከው ሶዳ ልትጨምርበት አትችልም ብሎ ጮኸበት እዚያ የነበረ ሰው ሁሉ ጓደኛዬን ዞሮ ተመለከተው ከእፍረት የተነሳ ፊቱ አሸቦ ሲመስል ይታይ ነበር ጓደኛዬ እጅ ከፍንጅ ከመያዙ በፊት ሶዳ መስረቁ ለእርሱ ከጥፋት የሚቆጠር አልነበረም ከተያዘም በኋላ ቢሆን ሶዳ መስረቅ ያን ያህል የሚያሸማቅቅ አይደለም ለምፅራባውያን የሚዋጥላቸው ባይሆንም ሶዳ ከመስረቁ ይልቅ እጅግ ያሳፈረው በአንድ ባለ አነስተኛ ደሞዝ ተቀጣሪ እጅ ከፍንጅ መያዙ ነበር ስለዚህ ውኀ እየቀዳሁ ነው በማለት ተግባሩን ለመካድ ሞከረ ከዚያም ብርጭቆውን በውኀ ሞልቶ ሄደ የሶዳው ቅላትና አረፋ ግን በግልፅ ይታይ ነበር በሌላ ጊዜ ደግሞ አንድ የአጎቴ ልጅ ኢንሹራንስ ሲያጭበረብር ተይዞ ከቤተሰቡ የነቀፌታ ውርጅብኝ ሲወርድበት ነበር ነገር ግን እርሱ ትረካውን አስቂኝ ወደሆነ ገጠመኝ በመቀየር እፍረቱን ለመሸፈን ሞከረ ብዙ ገንዘብ ማትረፍ እንዲችል ለኢንሹራንስ ኩባንያው ባለትዳር መሆኑን መናር አስፈላጊ መሆኑን እንዳመነ በመናገር ትረካውን ጀመረ ስለዚህ ከሚስቱ ጋር እንዴት እንደተገናኙ ሥራዋ ምን እንደሆነና የልደት ቀኗን የሚያስታውሰውን ገጠመኝ ሳይቀር ተናገረ አሁንም ድረስ ፓኪስታን አገር እንደምትኖርና ከዚህ የተነሳ የምስከር ወረቀት እንደሌለው ለድርጅቱ ተወካይ አሳወቀ የፈጠራ ታሪኩን እውነት በማስመሰል አውርቶ ኩባንያውን ካሳመነ በኋላ የመጨረሻ አነስተኛውን የከፍያ መጠን እንዲከፍል ተወሰነለት በዚህ ተግባሩ የተቆጣነው እኔና አንድ ሌላ የቤተሰብ አባል ብቻ ነበርን ሁለታችንም ደግሞ በአሜሪካ የተወለድን ነን ነገር ግን ታላላቆቹ እየሳቁ ኩባንያው በቂ ገንዘብ ስላለው እንዳንጨነቅለት ነገሩን የአጎቴ ልጅም በመስማማት ትረካውን ቀጠለ ከአንድ ዓመት በኋላ በመንገድ ላይ ግጭት ስለደረሰበት የኢንሹራንስ ኩባንያው ከፍያ እንዲፈፅምለት ጥያቄ አቀረበ ስልከ ደውሎ ስለ አደጋው በዝርዝር ሲያስረዳ ሳለ የኩባንያው ወኪል አደጋው በደረሰ ጊዜ ባለቤቱ አብራው መኖር አለመኖሯን ጠየቀው እርሱ ግን ሚስት እንደሌለችው ተናገረ አሁንም ወኪሉ ከዚህ ቀደም ሚስት አግብቶ እንደሆን ጠየቀው የአጎቴ ልጅም እንዳላገባ ተናገረ ከዚያ በኋላ ለኩባንያው ሲከፍል ከነበረው የኢንሹራንስ ዋጋ አጥፉን ተቀበሰ ቤተሰቡ በመላ በሳቅ መፍረስ ጀመረ ሲዋሸ የመያዙን አሳፋሪ ታሪከ ጎበዝ ተራኪ መሆኑን በማሳየት ከበሬታን አተረፈበት መልካም ነገር መሥራትም ሆነ የጥፋተኝነት ስሜት በስሌቱ ውስጥ አልተካተቱም ነበር በከብርና ውርደት ላይ የተመሠረተው የምስራቁ ባሕል በንፅህናና ጥፋተኝነት ላይ ከተመሠረተው የምዕራቡ ባሕል በተለየ ሁኔታ ነገሮችን እንዴት እንደሚያይ ለማስረዳት ያህል ነው እነዚህን ቀለል ያሉ ታሪኮች የጠቀስኩት በእርግጥ በእስልምና ውስጥ ጥልቅ የሆነ የሥነ ምግባር መርህ ይገኛል ስለዚህ ነገሩን በማቅለል ሙስሊሞች እጅ ከፍንጅ አስካልተያዙ ድረስ የፈለጉትን ነገር ያደርጋሉ የሚል የተሳሳተ አስተሳሰብ ውስጥ መግባት የለብንም ሆኖም የጥፋተኝነት ስሜት በምስራቁ ባሕል ውስጥ ከውርደት ያነሰ ግምት እንደሚሰጠው መናገር ይቻላል ወደ ሁለተኛ ትውልድ ምዕራባውያን ሙሰሊሞች ስንመጣ ደግሞ እነዚህን ሁለቱን ባሕሎች አብሮ ማስኬድ ምን ያህል ከባድ እንደሚሆን ማሰብ ይቻላል በማሕበረሰቡ ዘንድ እምብዛም ተቀባይነት የሌለውን ተግባር ሲፈፅም ከተገኘ ወጣቱ ሙስሊም በውስጡ የጥፋተኝነት ስሜት ስለሚሰማው ለመደበቅ ይሞከራል አፍረትን ለመሸፈን የሚደረገው የምስራቅ ልማድ የጥፋተኝነት ስሜት አንዲሰማው የሚያደርገውን የምዕራብ ባሕል ይሸፍነዋል ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ስበቃ ለእኔም ይህ ጉዳይ ችግር ሆኖብኝ ነበር ጓደኞቼ ሁሉ ሙስሊም መሆኔን ስለሚያውቁ በራሴ ምርጫ የፍቅር ጓደኛ መያዝ እንደማይፈቀድልኝ ያውቃሉ በቤተሰብ ምርጫ ማግባት አስደሳችና ጥሩ መሆኑን ለማስረዳት በመሞከር ለባሕሌ አምባሳደር ለመሆን ጥረት አድርጌያለሁ ሴቶችን የመቅረብ ፍላጎት አስካዳብር ድረስ ይህ ጉዳይ አምብዛም አላስጨነቀኝም ነበር የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለሁኝ ፍቅር ቢጤ ጀማምሮኝ ነበር ልጅቱም ደግሞ እንደምትወደኝ ትናገር ነበር በምዕራባውያን ባሕል መሠረት አጅ ለእጅ ተያይዞ የፍቅር ወሬዎችን ማውራት ተቀባይነት ያለው ነገር ነው ነገር ግን ከለመድኩት የምስራቅ ባሕል ጋር ስለሚጋጭብኝ ለማንም ሳልናገር ቆየሁኝ ስሜቱ ባይለቀኝም ከአንድ ሳምንት በኋላ ጉዳዩን እርግፍ አድርጌ ተውኩት ልጅቱ ትንሽ ቆይታ ከምርጥ ጓደኛዬ ከዴቪድ ጋር ጓደኝነት ጀመረች ለአርሷ የነበረኝ ስሜት በቀላሉ ስላልተፋታኝ ከቆይታ በኋላ የምርጥ ጓደኛዬን የሴት ጓደኛ በመመኘቴ የጥፋተኝነት ስሜት ይሰማኝ ጀመር ጓደኝነት ከመጀመራቸው በፊት ከአርሷ ጋር ምስጢራዊ ግንኙነት አንደነበረኝና አሁንም ድረስ ለእርሷ የሆነ ስሜት አንዳለኝ ለዴቪድ ተናዘዝኩኝ ለምን ይህንን ጉዳይ እንደደበቅኳቸው ከጓደኞቼ መካከል ሊረዳልኝ የቻለ ማንም አልነበረም ዴቪድ ጭራሹኑ እንቆቅልሽ ሆኖበታል ጉዳዩን ከእርሱ መደበቄና የሴት ጓደኛውን ፍቅር በልቤ ውስጥ ማስተናገዴ ከህደት ሆኖ ነበር የታየው ለምርቃት ጥቂት ጊዜ ሲቀረን በኔና በዴቪድ መካከል ከፍተት ተፈጥሮ ነበር በዚህም ምከንያት ከምቀርባቸው ሰዎች ሁሉ ተነጥዬ ብቸኛ ሆፔ ነበር አሁንም በድጋሜ ጓደኛ አልባ ሆኛለሁ ነገር ግን ልቤ በጣም ተሰብሮ ግራ መጋባት ውስጥ ገብቻለሁ ምንድነው የተፈጠረው። አኔ የማውቀው አስልምና ይህ አልነበረም በሩቅ አገራት የሚኖሩት ሙስሊሞች በአላህ ስም ከፉ ተግባራትን ሲፈፅሙ እሰማለሁ ነገር ግን ከሩቅ የሚሰሙ ወሬዎች እንደመሆናቸው መጣን በኔ ላይ ያመጡት ተፅዕኖ አልነበረም ይህኛው ግን በቤታችን አቅራቢያ የተፈፀመ ነው የገዛ ልባችንን የመታ ጥቃት ነበር በተከታዮቹ ሳምንታት የዜና ማሰራጫ ጣቢያዎች ሕንፃዎቹ ሲፈራርሱ ደጋግመው ማሳየታቸውን ተያያዙ ደግመው ደጋግመው ያሳዩታል በአምላኬ ስም በሺህዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን ሰዎች ሕይወት ሲቀጠፍ ተመለከትኩኝ በመጨረሻም ከልክ አለፈ ስለ እምነቴ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እውነቱን ማወቅ ይኖርብኛል የሰላም ሃይማኖት የሆነውን የኔን እስልምናና የሸብር ሃይማኖት የሆነውን የቴሌቪዥን አስልምና የማስታርቅበትን መንገድ ማግኘት ሊያስፈልገኝ ነው ከከስተቱ በኋላ አሥራ ሁለት ዓመታት ቢያልፉም ጥያቄው ፊት ለፊት ከሜታየው በላይ ውስብስብ መሆኑን ተረድቻለሁ ከግምት ውስጥ ሲገባ የሚገባው ትልቁ ነገር ይጓፅም ትርጓሜ ነው ዳፅሳምስንል የሙስሊሞችን እምነት ማለታችን ከሆነ ሰዎች ስለ እምነቱ በሚያስተምሩበት መንገድ ላይ ተመስርቶ የሰላም ወይም የሸብር ሃይማኖት ሊሆን ይቸላል በምዕራብ የሚኖሩ ሙስሊሞች በጣም ውሱን የሆነን የአስልምና ዓይነት ነው የሚማሩት ልክ እኔና ባጂ እንደተማርነው መሐመድ ራስን የመከላከል ጂሃድ ብቻ እንደፈፀመና በቁርአን ውስጥ የሚገኙት ነውጠኛ ጥቅሶች ውሱን የሆኑ ራስን የመከላከል አውዶችን ብቻ አንደሚያሳዩ ነው የሚማሩት ሯድ ሰላማዊና ከፉ መሻቶቻችንን ለማሸነፍ በውስጣችን የሚደረግ ትግል ተደርጎ ነው የሚተረጎመው ምዕራባውያን ሙስሊሞች ስለ እምነታቸው ሲጠየቁ በቅንነት የሰላም ሃይማኖት መሆኑን ይገልፃሉ በምስራቅ ሚኖሩት ሙስሊሞች ደግሞ ስለ እስልምና የተለየ አመለካከት አላቸው እስልምና ከሁሉም ሃይማኖቶችና የኑሮ ዘይቤዎች የላቀ እንደሆነና አላህ ይህ ሃይማኖት መላውን ዓለም ተቆጣጥሮ ማየት እንደሚፈልግ ነው የሚማሩት ሮ ብዙ ጊዜ የእስላምን ጠላቶች ለመታገል እንደሚደረግ አካላዊ ፍልሚያ ነው የሚያዩት እነዚህ ሰዎች ስለ እምነታቸው ሲጠየቁ እስልምና ዓለምን ሁሉ እንደሚቆጣጠር በቅንነት ይናገራሉ እስልምናን በተከታዮቹ አመለካከት መሠረት የምንተረጉም ከሆን የሰላም ሃይማኖት ሊሆንም ላይሆንም ይትላል ነገር ግን አስልምናን መሐመድ እአንዳስተረው የእምነቶችና የልማዶች ሥርኣት አድርገን ከተረጎምነው የትርጉሙ አከራካሪነት ይቀንሳል ቀዳሚያን የሆኑ የታሪከ ድርሳናት እንደሚያስረዱት መሐመድ የማጥቃት ወታደራዊ ዘመቻዎችን ፈፅሟል አንዲሁም ዓላማውን ከግብ ለማድረስ ነውጠኝነትን ተጠቅሟል ጀሃድዮ የሚለውን ቃል መንፈሳዊና አካላዊ ትርጉም የሰጠው ቢሆንም በአካላዊ ገፅታው ላይ ይበልጥ አተኩሯል ሰላማዊው የአስልምና ልምምድ ብዙ ጊዜ የተመሠረተው የቅርብ ጊዜና በተለይም በምዕራባውያን የመሐመድ ትምህርት አተረጓጎም ላይ ሲሆን የበለጠ ነውጠኛ የሆነው እስልምና ደግሞ በትከክለኛውና ታሪካዊው አተረጓጎም ላይ የተመሠረተ ነው በእርግጥ አንደማንኛውም ሰው በምዕራብና በምስራቅ የሚኖሩት ሙስሊሞች የተማሩትን ነው የሚያምኑት ታሪካዊ ዳራዎችን የበለጠ በጥልቀት የማጥናት ጥረት የሚያደርጉት የተወሰኑት ብቻ ናቸው አነዚህ ጥቂት ሰዎች ደግሞ ልከ እኔ በቲኦኬ ከፍለ ጊዜ አደርግ እንደነበረው ቀደም ሲል ያመኑትን ነገር ለመከላከልና ከዚያ በተፃራሪ የሚያሳዩ መረጃዎችን ችላ ማለት ወይም አሳንሶ የማየት ጥረት ያደርጋሉ እኔ እንደዚያ ነበርኩኝ በውስጣዊው እኔነቴ የእስልምናን ትከከለኛ ገፅታ ለማወቅ አፈልግ ነበር ነገር ግን ምርመራዎችን በማድረግ የልጅነት አምነቴን መፈተሸ ከባድ ነበር አስቸጋሪ የሆኑ እውነታዎችን ችላ የምልባቸውን መንገዶች እፈልግ ነበር አድሎዬን ይዝ እንዳልቀጥል የሚያደርገኝ ነገር ያስፈልገኝ ነበር ደካማ የሆኑ ሙግቶቼን ዳግመኛ ዞር ብዬ እስከማላያቸው ድረስ ደግሞ ደጋግሞ በፊቴ ድባቅ የሚመታ ማስረጃ ያስፈልገኝ ነበር አመለካከቴን መገዳደር የሚችል የማያመቻምች አስተዋይ ሙስሊም ያልሆነ ጓደኛ ያስፈልገኝ ነበር በጣም ድፍረት ያለውና ግትር መሆን አይጠበቅበትም ነገር ግን በሕይወቴ ውስጥ ትልቅ ቦታ የምሰጣቸውን ነገሮች ላወራው የምቸለው ለእኔ የታመነና የተወደደ ሰው መሆን ያስፈልገዋል እግዚአብሔር ከዚህ ሰው ጋር የመተዋወቅ ዕድል ለኔ መስጠቱና ሕይወቴን እስከወዲያኛው ሊለውጥ የሚቸለውን መንገድ መጀመሬ አልገባኝም ነበር ማረ ሟፇሳዕርረግያምምርሮፖ መዲዳጓጋዬፖ ደራፈ ፈያ ሁለገብ ከርስቲያን ቦዖሟሐው ጋወ ዖሟሮረዕ ፇምሂረ ይሂጋጀ ናኙው ሰ ዎፖጎራዎ ና ምህሪራሇ ያሟጋሪቃ ያሃ ሪው ይሃሄው ደፇዎ ለዕሥፖዎአያሥ ማሮ ፖይልፖጾ ድረሪ ይያቻ። ብዬ ራሴን አጠይቃለሁ ሰዎችን በመልካም አቀራረብ በመቅረብ ሰላምታ እየሰጡ ችግራቸውን ተካፍለው አብረው የሚጸልዩና መልዕከታቸውን የሚያስተላልፉ የመንገድ ዳር ሰባኪዎች መኖራቸውን አውቃለሁ ነገር ግን አንድም ቀን አላጋጠሙኝም ያጋጠሙኝ ሰዎች ዝም ብለው መንገድ ዳር በመቆም ስለ እምነታቸው የሚናገሩ ናቸው እንደዚህ ዓይነት ሰባኪዎች ጥቂቶችን እንደሚደርሱና ብዙዎችን ግን አሰናከለው ወደ ኋላ እንደሚመልሱ ምንም ጥርጥር የለውም እንዳለመታደል ሆኖ ብዙ ከርስቲያኖች ወንጌልን ስለማድረስ ተመሳሳይ አመለካከት አላቸው ከአድማጫቸው ጋር ሳይግባቡና ሐሳቡን ሳይሰሙ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ስለ ከርስትና እምነት ይናገራሉ ወንጌል መሠረታዊ የሆነ የኑሮ ለውጥን የሚፈልግ ነው ነገር ግን ብዙዎች የማይግባቧቸው ሰዎች ሕይወታቸውን እንዲለውጡ ቢነግሯቸው ለመስማት ስለማይፈልጉ የጥድፊያ ወንጌል ስርጭት አያዋጣም ስለዚያ ሰው ሕይወት ምንም የሚያውቁት ነገር አይኖራቸውምና በሌላ ወገን ደግሞ እውነተኛ ጓደኛ ከልብ በመነጨ ቅንነት የጓደኛውን ሁኔታና የሕይወት ትግል በማጤን ተመሳሳይ መልዕከት ቢናገር መልዕከቱ ግልፅ ሆኖ ጎላ ብሎ ይደመጣል ውጤታማ የወንጌል ስርጭት በመግባባት ላይ የተመሠረተ ነው ጥቂት የሆኑ ልዩ ሁኔታዎች ግን ይኖራሉ የኔን ሁኔታ ብነግራችሁ ስለ ግል ሕይወቴ ከልቡ የሚያስብ አንድም ከርስቲያን አልገጠመኝም ነበር በከፍታም ሆነ በዝቅታ የሕይወቴን ሸከሞች የተካፈለ አንድም አልነበረም ከብዙ ከርስቲያኖች ጋር ተዋውቄያለሁ አርግጠኛ ነኝ ከርስቲያን ብሆን ኖሮ ጓደኞቸ ይሆኑኝ ነበር ነገር ግን ያ ዓይነት ጓደኝነት በሁኔታ ላይ የተመሠረተ ነው ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ስለ ሕይወት ግድ የሚላቸው ክርስቲያኖች አላጋጠሙኝም ማንም ስለ እኔ ግድ የሚለው ከርስቲያን ስላልነበረ እኔም ስለ መልዕከታቸው ግድ አልነበረኝም ነገር ግን ያ ሁኔታ የሚለወጥበት ጊዜ ቀርቦ ነበር ከ በኋላ ሕይወት የቀድሞ መልኳን ለመያዝ ጥቂት ሳምንታት ማለፍ ነበረባቸው ባጂና እኔ ትምህርታችንን ከእንደገና ቀጥለናል አባ ወደ ሥራ ተመልሷል እማም ገበያ ለመሄድ የነበራት ፍርሃት እየረገበላት ነው አሁንም ድረስ ሙስሊሞችን በጥርጣሬ የማየቱ ሁኔታ አንደቀጠለ ቢሆንም አስልምናም በዜና ማሰራጫዎች ቢብጠለጠልም በስሜታዊነት ተነሳስቶ ጥቃት የመፈፀም ሁኔታ የፈራነውን ያህል አልነበረም መስጊዳችን መጠቃቱና በተደጋጋሚ ፀረ ሙስሊም ንግግሮች መሰማታቸው እውነት ቢሆንም በሙስሊሞች ላይ የደረሰ አካላዊ ጥቃት መኖሩን አልሰማንም ፈራ ተባ እያልንም ቢሆን ወደ ቀድሞ ሕይወታችን እየተመለስን ነው የምርምር ቡድናችን በውድድር ላይ የሚሳተፍበት ጊዜ ቀርቦ ነበር በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከሚደረጉት ውድድሮች በተለየ ሁኔታ የኮሌጅ የምርምር ውድድሮች ለብዙ ቀናት የሚደረጉ ናቸው ብዙ ጊዜ ደግሞ በሌሎች ግዛቶች ነበር የሚደረጉት የኛ ቡድን ለመጀመርያ ውድድሩ ወደ ቸስተር ፔንሲልቬንያ ነበር ያቀናውበጉዚችን ፅለት እማ እስከ ኦዲዩ ድረስ ሸኘችኝ ፊጋ ለረርሃዕ ድ ፊፖርረነዕ የተሰኘው ሕንፃ ጋር ስንደርስ ለውድድሩ ከሚጓዙት ተማሪዎች መካከል አንዱ ሊቀበለን መጣ ከዚህ ቀደም በልምምድ ቦታ ላይ አንድ ሁለት ጊዜ አውርተናል ነገር ግን ብዙም አንተዋወቅም ነበር ወደኛ በፈጣን እርምጃ በመምጣት ሻንጣዬን እያገዛኝ ለአማ ራሱን አስተዋወቀ ሰላም እመቤት ቁሬሺ ዴቪድ ዳዊት እባላለሁ አማ ወደማታውቀው ቦታ እኔን ከመሸኘቷ በፊት ከቡድኑ አባላት መካከል አንድ ሰው በመተዋወቋ በጣም ደስ ብሏታል ሰላም ዳዊት ስላገኘሁህ በጣም ደስ ብሎኛል ከነቢል ጋር ትጓዛለህ። ይህንን ጉዳይ በጥልቀት ካላየኸው ለኔ ጥሩ ግምት አልሰጠኸኝም ማለት ነው ጊዜ ሳታጠፋ መረጃዎችን ማገላበጥ መጀመር ይኖርብሃል ተነስቼ ወደ ሻንጣዬ እየሄድኩኝ አታስብ ከአሁን ጀምሮ ተጀምሯል አልኩት ልብሶቼን አውጥቼ ስጨርስ ለውድድሩ የመጨረሻውን ዝግጅት ማድረግ ጀመርን ከአፍታ በኋላ ስለ ውይይታችን ማሰብ ጀመርኩኝ አሁንም ድረስ መጽሐፍ ቅዱስ መበረዙን አርግጠኛ ነበርኩኝ ነገር ግን ከዚህ ቀደም ከሰማኋቸው ይልቅ ጠንከር ላሉ ሙግቶች መልስ መስጠት ነበረብኝ ወደ ቤት ተመልሼ እነዚህን ነገሮች በጥልቀት ማጥናት እንዳለብኝ ወሰንኩኝ ምዕራፍ ሃያ ሁለት የጽሑፎች ዝግመተ ለውጥ ከጥቂት ቀናት በኋላ ወደ ትምህርት ቤት ተመልሰን ትምህርታችንን ቀጠልን ዳዊት ሥነሕይወትና ፍልስፍናን ደርቦ የሚያጠና ሲሆን እኔ ደግሞ የቅድመ ሜዲካል ተማሪ ነበርኩኝ ከዚህም የተነሳ የኬሚስትሪና የዝግመተ ለውጥ ሥነሕይወት ኢሾሉሽን ባዮሎጂ ትምህርቶችን በጋራ እንወስድ ነበር አንዳንድ ጊዜ በአንድ ከፍል ውስጥ አብሮ መማር እንዴት ጥሩ ነው ዳዊትና እኔ በመረዳዳት መንፈስ ኬሚስትሪን በጋራ እናጠና ነበር ነገር ግን በመካከላችን ፉከከር ነበር ከፈተና በኋላ መምህራኖቻችን የፈተና ውጤቶችን ሲለጥፉ እኔና ዳዊት ውጤታችንን ለማየት እርስ በርሳችን አንጋፋ ነበር ከጓደኝነት ፉክክራችን የተነሳ እኔና ዳዊት ሁል ጊዜ ከከፍሉ ከፍተኛ ውጤት እናስመዘግብ ነበር አንዳንድ ጊዜ ደግሞ በአንድ ከፍል ውስጥ አብሮ መማር ጥሩ አይደለም በዝግመተ ለውጥ ሥነሕይወት ከፍለ ጊዜ አኔና ዳዊት ትኩረት ሰጥቶ ለመማር እንቸገር ነበር አስተማሪዋ በፈጣሪ መኖር እንደማታምን በግልፅ ትናገር ስለነበር አንዳንዴ ጣል በምታደርጋቸው አስተያየቶች ሐሳባችን ከዋናው ትምህርት ላይ ይሰረቅ ነበር ጠንካራ አማኞች አንደመሆናችን መጠን አብዛኞቹ የአምላክ የለሾች አስተያየቶች ደካማ ሆነው ይታዩን ነበር አስተማሪያችን ለአምላከ የለሽነት ያደላ አስተያየት በሰጠች ቁጥር አንዳችን ወደ ሌላችን ዞረን በተናገረቸው ነገር መነሻ ወይም በእርሷ ሁኔታ አንቀልድ ነበር መቸስ የኮሌጅ ልጆች አንደመሆናችን መጠን አይፈረድብንም አንድ ቀን አምላከ የለሽነትን የሚሰብከ አጭር ንግግር ካደረገች በኋላ ስለ ታከሶኖሚ ማለትም እንስሳትን በዝርያቸው ስለመከፋፈል ማስተማር ጀመረች ከዚያ ወደ ዳዊት ጠጋ ብዬ ከብዙ ጊዜ ጥናት በኋላ የዚህች ሴትዮ ፀጉር የራሱ ሕይወት አለው ብዬ ደምድሜያለሁ በየትኛው የሕይወት ቤተሰብ መመደብ እንዳለብኝ እያሰብኩ ነው። ከርቲያኖች ከርስቲያን ያልሆኑ የፈለከውን መጥራት ትትላለህ ቀደም ሲል እንዳልኩት ሌሎች አሳማኝ የሆኑ ምክንያቶች አሉ ለምሳሌ ያህል ኢየሱስ በመስቀል ላይ መሞቱን የሚመሰከሩ ከኢየሱስ በኋላ በመጀመርያው ከፍለ ዘመን የተጻፉ ከርስቲያናዊ ያልሆኑ ምንጮች አሉ ይህንን ደግሞ የሚያረጋግጡ ጉልቁ መሳፍርት የሌላቸው ከርስቲያናዊ ምንጮች አሉ በተጨማሪም ለረጅም ዘመናት ይህንን የሚፃረር ትውፊት የለም ነገር ግን ጥያቄህን ለመመለስ ስለ ሁሉም ነው እየተናገርኩ ያለሁት ማይከ የመጨረሻ ቃሉን አከለ ሊቃውንት በዚህ ላይ ሙሉ በሙሉ ይስማማሉ ኢየሱስ በመስቀል ላይ መሞቱ በጣም ከተረጋገጡት የታሪከ አውነታዎች መካከል አንዱ ነው የተባለውን በጥሞና ሰምቼ ዋጥኩት አባም ለመሄድ ጊዜው እንደሆነ ጠቆመ ትንሽ ቆይቼ ለመወያየት ፈልጌ ነበር ነገር ግን አባ ፈቃደኛ አልሆነም ወደ ቤት ስንሄድ የነበረው ፀጥታ የማይከን የመጨረሻ ቃላት የሚያስተጋባ ነበር እስልምና ስለ ኢየሱስ ስቅለት የሚያቀርባቸውን ትወራዎች የመተካካት ትወራ ወይንም ደግሞ ራስን የመሳት ትወራ ይዝ መቀጠል የሚኖርብኝ ከሆነ ታሪከን መፃረር እንደሚኖርብኝ ይሰማኝ ጀመር ቁርአን ግን ማስረጃዎችን በጭፍን በመካድ በአምነት ብቻ እንድቀበለው ይጠብቅብኛል የሊትመስ ወረቀት ፈተናችን ይህ ነው ምንም የሚያምታታ ነገር ደግሞ የለም የክርስትና ሐሳብ ከማስረጃዎች ጋር መቶ በመቶ ይስማማል ከዚህ የከፋው ደግሞ አባ በሙግት ሲረታና እጅ ሲሰጥ ማየቴ ነው በውይይታችን ወቅት በአንድም ሆነ በሌላ ምከንያት በግልፅ የተቀመጠውን ማስረጃ አይቼዋለሁ ይህ ደግሞ በአጅጉ ምቾት ነስቶኛል ወላጆቼ ያስተማሩኝን ሳልመረምር ዝም ብዬ ማመን እንደሌለብኝ ተገንዝቤያለሁ ቅንነታቸውን ትጋታቸውን ወይም ፍቅራቸውን አልጠራጠርም ነገር ግን እውነትን መረዳታቸውን መጠራጠር ጀምሬያለሁ የእርግጠኛነት መጋረጃ የተገፈፈልኝ ይመስል ነገሮችን በተለየ ብርሃን ማየት ጀምሬያለሁ ዕድሜ ልኬን ባለቀለም መነፅር ሳደርግ ኖሬ ለመጀመርያ ጊዜ የወለቀልኝ ያህል ተሰማኝ ሁሉም ነገር ከበፊቱ የተለየ ሆኖ ታየኝ ሁሉንም ደግሞ ከመሠረቱ በጥንቃቄ መመርመር እንዳለብኝ አመንኩኝ ምናልባት ምናልባት የከርስትና መልዕከት እውነት የመሆን ጠባብ ዕድል ይኖረው ይሆናል ምዕራፍ ሃያ ስድስት በቤተ ክርስቲያን የተገኘ ሙስሊም ቤት ስንደርስ እማ በር ላይ ተቀበለችን ውይይቱ እንዴት እንደነበር ለማወቅ ጓጉታለች ሐሳባችንን በተሳካ ሁኔታ ማቅረባችንን አፅንዖት በመስጠት ስለ ውይይቱ አጭር ዘገባ አቀረብኩላት አባ አሁንም ድረስ አንደበቱ መቆለፉንና እኔም ከፍሉን ለቅቄ ለመውጣት መጣደፌን ካየች በኋላ የነገርኳትን ማመኗን እጠራጠራለሁ ሰበብ ፈጥሬ በጥድፍያ ወደ ላይኛው ደረጃ ወጣሁ ሁለተኛው ደረጃ ላይ የሚገኘው ሰፋ ያለ ከፍል መጀመርያ የታሰበው እቃ ማስቀመጫና ማጠብያ ከፍል እንዲሆን የነበረ ቢሆንም አባዬ ግን ሰፋ ያለ የመኝታ ከፍል አንዲሆን አድርጎ አስገነባው ኋላ ላይም በመጽሐፍት የተጠቀጠቀ ቤተ መጻሕፍት አደረገው ስለ ሃይማኖት ማንበብ ስፈልግ በመጽሐፍት ከተሞሉት መደርደርያዎች መካከል ወደ አንዱ በመሄድ የምፈልገውን መጽሐፍ መዝዝ በሆዴ ተኝቼ አነባለሁ ብዙ ጊዜ ለመዝናናት የማደርገው ነገር ነው ዛሬ ግን ስለ መዝናናት አይደለም እያሰብኩ ያለሁት በልቤና በአእምሮዬ ውስጥ የነገሠውን ውጥረት የማርገብ ተልዕኮ ይዢ ነው የመጣሁት ስለ ኢየሱስ የተጻፉትን በመደርደርያዎቹ ላይ ያሉትን መጻሕፍት በሙሉ አወጣኋቸው ሁሉም በሙስሊም ምሐራን የተጻፉ ናቸው ማለት ይቻላል ቀደም ሲል ለሰማኋቸው ሙግቶች መልስ ፍለጋ ገፆቹን በርዕስ መግለጥ ተያያዝኩኝ በዚህ ወቅት ነበር ለመጀመርያ ጊዜ አንድ ነገር ያስተዋልኩት ስለ ኢየሱስ የሚያወሩት የአባዬ መጻሕፍት ሁሉ ከርስትናን ለማጥቃት ታልመው የተጻፉ ናቸው ገና ከጅምራቸው የድምዳሜ ሐሳብ ያቀርባሉ ከዚያም ያንን ድምዳሜ የሚደግፉ ሐሳቦችን ይለቃቅማሉ ከዚያም ሙግታቸውን ያቀርባሉ ጌሪ የአባን ሙግት በተመለከተ እንደተናገረው ሁሉ ጥናቶቹ በጥንቃቄ ወይም በገለልተኝነት የተደረጉ አይደሉም ሙግታቸውን ውድቅ ለሚያደርጉ ማስረጃዎች መልስ አይሰጡም ይህ ደግሞ ሙግታቸውን ያልተፈተነና ልፍስፍስ ያደርገዋል ሙግታችን በተደጋጋሚ ውድቅ ሲሆን ብመለከትም ነገር ግን ይህ የሆነበት ምከንያት የጥናት አካሄዳችን ደካማ በመሆኑ ብቻ እንደሆነ አምኛለሁ ምስራቃውያን ጸሐፍት በጥልቅ ስሜታዊነት ላይ የተመሠረቱና ልብን የሚመስጡ ሙግቶችን ማቅረብ ቢችሉም ምዕራባውያን ግን የበለጠ ሥልታዊ በሆነ መንገድ ማሰባቸውና ምላሽ የሚሆኑ ግሩም ሙግቶችን በማቅረብ የታጠቁ መሆናቸው የበላይነትን እንዲቀዳጁ ያደርጋቸዋል የምዕራባውያኑን ሥልት ከምስራቃውያኑ ስሜት ጋር ባጣምር የበለጠ አሳማኝና ፈተናዎችን ማለፍ የሚችል ሙግት ማቅረብ እችል ይሆናል በአካሄዴ ሥልታዊነትን ለመከተል ጊዜው እንደሆነ ተሰምቶኛል ነገር ግን እንዴት መጀመር እንዳለብኝ ምንም የማውቀው ነገር አልነበረኝም ብዙም ሳይቆይ ዳዊት ደወለ ስልኬን አውጥቼ አየሁት ነቢል አለ ጫወታ በሚንፀባረቅበት ድምፀት ስለ ውይይቱ ምን ትላለህ ስካሁን እያሰላሰልኩት ነው ሥልታዊ አጠናን መማር አንደሚያስፈለልገኝ ይሰማኛልለ እውነትህን ነው። ማይከና ጌሪን ለሁለተኛ ጊዜ ባገኛቸው ቤተሰቦቼ እንደተቀበልኳቸውና በእነርሱ ለመመራት ዝግጁ እንደሆንኩ ያስባሉ በተለይም አባን ወደ ውይይቱ ካልጋበዝኩት ደግሞ ጉዳዩ ይጎላል እርሱን መጋበዝ ደግሞ የማይመስል ነው እርሱ ከእኔ ጋር የሚመጣ ከሆነ በነፃነት መናገር አልችልም የሚጨነቁበትን ምከንያት ላቀብላቸው አልፈልግም እውነቱን በመናገር ደግሞ እንዳልሄድ እንዲከለከሉኝ በር መከፈትም አልፈለኩም ከዳዊት ጋር ለመዝናናት እንደምሄድ ልነግራቸው ወሰንኩኝ ይህ አውነት ቢሆንም ነገር ግን ግማሽ እውነት ነበር በቀጣዮቹ ዓመታት ሙሉ በሆነ እውነትና በግማሽ አውነት መካከል ወዲያና ወዲህ በመቅዘፍ የግበረ ገብነት ልኬቴን መፈታተን ነበረብኝ ይህንን ያደረኩት ደግሞ አስገዳጅ ሁኔታዎች ስለገጠሙኝና ለተሻለው መልካም ነገር ስል ነበር ሁኔታው ባያስደስተኝም ከመራራና ከጎምዛዛ መምረጥ ስለነበረብኝ ይህንን ለማድረግ ተገድጃለሁ በቀጣዩ ቀን ወደ ዳዊት ቤት ሄድኩኝ አርሱም ወደ ቤተ ክርስቲያን ወሰደኝ ካምፓስ ኢምፓክት የተሰኘ የኮሌጅ ቤተ ከርስቲያን ነበር ለኔ ሙሉ በሙሉ እንግዳ የሆነ ሁኔታ ነበር በመድረኩ ላይ የአምልኮ ቡድን ብለው የሰየሟቸው ሰዎች ነበሩ ጊታር ጃዝና ሌሎች የሙዚቃ መሣርያዎችን እየተጫወቱ ይዘምራሉ ሕዝቡም እያጨበጨበ አብሯቸው ይዘምራል አስቂኝ የሆኑ ማስታወቂያዎች ነበሩ ሰዎች ደግሞ ሰላምታ የሚለዋወጡበት አጭር የእረፍት ጊዜ ነበር የገንዘብ መሰብሰብያ ከረጢቶችም በጉባኤው ውስጥ ይዘዋወሩ ነበር ከዚህ ቀደም እንዲህ ያሉ ነገሮችን አይቼ ስለማላውቅ ምንም አልጣመኝም ነበር አምልኮ ማለት በሰውና በፈጣሪ መካከል የሚደረግ የግል ጉዳይ ነው ነገር ግን አነዚህ ሰዎች ከበሮ ይደልቃሉ ገንዘብም ደግሞ ይጠይቃሉ በመስጊድ ሁሉም ሰው በፈጣሪው ላይ ብቻ እንዲያተኩር ተብሎ ማንም ሰው በአምልኮ ሰዓት ፊታቸሁ ቆሞ አይጋርዳችሁም ሴቶች ደግሞ በአምልኮ ሰዓት መድረከ ላይ መቆማቸው ገደብ የጣሰ ተግባር ነው ስለዚህ የአምልኮ ጊዜው በጣም ረብሾኛል ምኑም አልጣመኝም ነበር ለከርስቲያኖች እግዚአብሔርን ማምለክ ማለት ትርጉሙ ይህ ከሆነ ይቅርብኝ ብዬ ለራሴ አሰብኩኝ ለኔ ትልቁ ጉዳይ ስብከቱ ነበር ጌሪ የመናገርያ ጊዜው ሲደርስ ግብረ ገብነት ስለማጣት ተናገረ ከዚያም የኢየሱስ ትንሣኤ በታሪካዊ ማስረጃ ሊረጋገጥ የሚችልና ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን አብራራ ሞት የሕይወት ማከተሚያ እንዳልሆነና ሕልውናችን እንደማይጠፋ ተናገረ ይህ ደግሞ ከሞት በኋላ ሕይወታችን ምን አንደሚገጥመው በማሰብ እንድንደሰት ወይም እንድንጨነቅ የሚያደርገን ነገር ነው ነገር ግን ጌሪ በተናገረው መሠረት የኢየሱስ ትንሣኤ ለዚህ ምላሽ ሰጥቷል የከርስትና መልዕከት እውነት መሆኑንና ኢየሱስን እንደ ጌታና አዳኛችን ካመንነው ለዘለዓለም ከእግዚአብሔር ጋር በሰማይ እንደምንኖር ያረጋግጣል በዚህ ጊዜ ነበር ሙስሊም የሆነው አእምሮዬ ከጌሪ ጋር መስማማት የቸገረው እውነት ነው ፈጣሪያቾቸን ኢሟቲያን አድርጎናል አካላችን ቢሞትም የነፍሳችን ህልውና ይቀጥላል ነገር ግን ኢየሱስ ከዚህ ቀደም ከሞት ተነስቶ ቢሆን እንኳ ከርስትና የሚያስተምረው እያንዳንዱ ነገር አውነት እንዲሆን አያደርገውም ከቤተ ከርስቲያን አንደወጣን ዘማከስ ወደ ተሰኘ ሬስቱራንት አቀናን እኔም ሰላጣ እያላመጥኩ መናገር ጀመርኩኝ ሜሪ እስኪ የኢየሱስ ትንሣኤ አውነት ነው እንበል ይህ ከመቅፅበት አንደ ጌታና አዳኝ ልንቀበለው ይገባል ማለት አይደለም በቃ ሞቶ ነበረ ከሞት ተነሳ ማለት ነው። ሼኽ ብዙ ጊዜ በአስልምና ሶሲሊሙ ተሟጋች ሻቢር አሊ ከቶሮንቶ የመጣ እጅግ ሥነ መለኮት የተመረቀ ዕወቅ የሆነ ሰው ነበር መድረከ የመያዝ ብቃቱ ከፍተኛ ሙስሊም መሪ ስለነበር አድናቂው ነበርኩኝ አስተውሎት የተሞላበት አቀራረቡ ከ የሸብር ጥቃት ወዲህ በሙስሊሞች ላይ የተፈጠረውን አሉታዊ አመለካከት ለመዋጋት መልካም አስተዋፅዖ አበርከቶ ነበር ዘወትር የሙስሊም ኮፍያውን ያለ ምንም መሸማቀቅ አጥልቆ ይታይ ነበር ረጅም ጥቁር ጢምና በሙስሊሞች ባሕል ውስጥ የተለመደው ሰፊ ቀሚስ መለያው ነበር አሕመዲ ባይሆንም የተወሰኑ የአሕመዲ ሙግቶችን ስለሚጠቀም በኔ ዕይታ የተዋጣለት ተሟጋች ነው ከርከሩ ከመጀመሩ በፊት ዳዊት ሻቢርን ከተማውን የማስጎብኘት ዕድል ገጥሞት ነበር ፖ ለፉ ሬፀይፅ የተሰኘውን የሜል ጊብሰን ፊልም እንዲያሳየው ሻቢር ዳዊትን ስለጠየቀው በሬጀንት ዩኒቨርሲቲ ወደሚገኘው የከርከሩ አዳራሽ ከመሄዳቸው በፊት በጋራ አይተውት ነበር ሻቢር ጥቂት ማረፍ ስለነበረበት ዳዊት ቀደም ብሎ በመምጣት በአዳራሹ ውስጥ የሚገኘውን የተሻለ ወንበር ያዘቡ ጌሪ ከርከሩን ለመታደም ወደ ከተማይቱ ተመልሶ ስለመጣ ወደ አዳራሹ ከመግባታችን በፊት ጥቂት አብረን ቆይተናል ከአፍታ በኋላ በጌሪና በዳዊት መካከል ተቀምጩ በሰባት መቶ ሰዎች በታጨቀው አዳራሽ ውስጥ የሚደረገውን ከርክር መከታተል ጀመርኩኝ ማይከ ለውይይት የሚጋብዝ አቀራረብ ያለው ሰው ነው እምነቱን የፈተሸበት ጊዜ እንደነበረና ወላጆቹ የነገሩትን ነገር በጭፍን ከመቀበል ይልቅ ስለ ሕይወትና ስለ እግዚአብሔር እውነቱን ለማወቅ ፍለጋ እንዳደረገ በመናገር ነበር የጀመረው የሚያካፍለው መረጃ ከርስትና እውነት መሆኑን እንዳሳመነው ተናገረ እኔም በተመሳሳይ የሕይወት አጋጣሚ ላይ ስለነበርኩኝ ይህ ንግግሩ በእጅጉ ቀልቤን ገዛው በትንሣኤ አስፈላጊነት ላይ አፅንዖት በመስጠት ንግግሩን ቀጠለ የኢየሱስ ትንሣኤ በእጅጉ ወሳኝ የሆነበት ምክንያት የከርስትና እውነት በዚህ ከስተት ላይ የተንጠለጠለ በመሆኑ ነው የኢየሱስ የቤዛነት ሞት ከታወቀበት ጊዜ ጀምሮ የከርስትና መሠረት ሆኖ ቀጥሏል ስለዚህ ኢየሱስ ከሙታን ካልተነሣ መሠረቱ ስለሚናጋ ከርስትና ውሸት ይሆናል በሌላ ወገን ደግሞ ኢየሱስ በአውነት ከሙታን ከተነሣ ከርስትና እውነት መሆኑን ለማመን የሚያስቸል በቂ ምከንያት አለ ለዚህ ነው የዛሬው ከርከር ከትምህርታዊ ርዕሰ ጉዳይ ውይይት በእጅጉ የላቀ የሚሆነው ለራሴ እንዲህ ብዬ አሰብኩኝ እውነትህን ነው ማይከ ከርስትና የተመሠረተው በትንሣኤ ላይ ነው እውነቱን ማወቅ የሚፈልጉ ነፍሶች አሉ ሙግትህ አሳማኝ መሆን አለበት ስለ ማይከ ሙግት ሁለት ሊካዱ የማይችሉ ጉዳዮች አሉ ታሪካዊ መሠረት አለው አንዲሁም ግልፅ ነው ሙግቱን በግልፅ አስቀምጦታል በዚህ ምሽት ጠንካራ ማስረጃ ያላቸውንና በአብዛኞቹ ምሑራን ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውን ሦስት እውነታዎች አቀርብላችኋለሁ ለእነዚህ ሦስት እውነታዎች የተሻለው ማብራርያ ደግሞ ኢየሱስ ከሞት ተነስቷል የሚል ነው የመጀመርያው እውነታ የኢየሱስ በመስቀል ላይ መሞት ነው ኢየሱስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ መሞቱ ጉዳዩን በሚያጠኑ ሊቃውንት ሁሉ ዘንድ መቶ በመቶ የሚታመን ነው እያንዳንዱን እውነታ በጠቀሰ ቁጥር ማይከ ማስረጃ ያቀርብ ነበር ኢየሱስ በመስቀል ላይ መሞቱን በተመለከተ እርሱና ጌሪ ከአስራ ስምንት ወራት በፊት ያቀረቡልኝን ማስረጃዎች ነበር ያቀረበው ይህም አሳቃቂ የሆነውን ግርፋትና ኢየሱስ በመስቀል ላይ መሞቱ በብዙ ምንጮች ውስጥ መጠቀሱን ያጠቃልላል የመስቀል ሞትን በተመለከተ ያለው ታሪካዊ ማስረጃ ከግምት ውስጥ ሲገባ በዚህ ዘመን የሚገኙት የኅከምና ባለሙያዎች ኢየሱስ መሞቱን አእንደማይጠራጠሩም አከለ የመጀመርያውን እውነታ በበቂ ማስረጃ ካረጋገጠ በኋላ ማይከ ወደ ሁለተኛው አለፈ እውነታ ሁለት መቃብሩ ባዶ ነበር በሚያስገርም ሁኔታ ጉዳዩን ካጠኑት ሊቃውንት መካከል ሰባ አምስት ከመቶ የሚሆኑት መቃብሩ ባዶ መሆኑን ይቀበላሉ ከስቅለቱ ከጥቂት ቀናት በኋላ መቃብሩ ባዶ እንደነበረ የሚያሳምኑ ብዙ ምከንያቶች መኖራቸውን ማይከ አስረዳ የመጀመርያው ምከንያት የከርስትና እንቅስቃሴ የተመሠረተው ኢየሱስ በመነሣቱና ሕያው በመሆኑ ላይ ነው ከርስትና የተጀመረው በኢየሩሳሌም በመሆኑ የኢየሱስ አስከሬን መቃብር ውስጥ ቢሆን ኖሮ የአይሁድ መሪዎች አስከሬኑን በከተማይቱ ውስጥ እየጎተቱ በማሳየት የከርስትናን አንቅስቃሴ መቅጨት በቻሉ ነበር ይህንን አለማድረጋቸው የኢየሱስ መቃብር ባዶ ስለመሆኑ ጠንካራ ማሳያ ነው መቃብሩ ባዶ ስለመሆኑ ሌላው ማሳያ አይሁድ ስለ ትንሣኤ ያላቸው አመለካከት ነው አብዛኞቹ አይሁድ በአካላዊ ትንሣኤ ያምናሉ የሞተው ያው አካል ተነስቶ ኢሟቲ ወደ ሆነ አካል እንደሚለወጥ ነው የሚያምኑት ደቀ መዛሙርቱ የኢየሱስን ትንሣኤ ሲናገሩ አካሉ እንደገና ሕይወት መዝራቱን መናገራቸው በመሆኑ በተዘዋዋሪ መቃብሩ ባዶ መሆኑን ያሳያል ሦስተኛው ምከንያት ከአይሁድ መሪዎች ጋር የተያያዘ ነው ስለ ኢየሱስ ሲጠየቁ ደቀ መዛሙርቱ አስከሬኑን እንደሰረቁ በመናገር በተዘዋዋሪ መቃብሩ ባዶ መሆኑን አምነዋል ይህንን ነጥብ ሲያጠቃልል ማይከ የኦከስፎርድ ፕሮፌሰር የሆነውን ዊልያም ዋንድ የተሰኘ ምሑር ጠቀሰ ያሉን ጠንካራ የሆኑ ታሪካዊ ማስረጃዎች ሁሉ መቃብሩ ባዶ መሆኑን ያሳያሉ ይህንን የማይቀበሉ ምሑራን ሳይንሳዊ በሆነው የታሪከ ምርምር ላይ በመመሥረት ሳይሆን በሌላ ምክንያት መሆኑ መታወቅ አለበትች። ይላል በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ማከዱዌል አዲስ ኪዳን ኢየሱስ አምላከ መሆኑን እንደሚያስተምር ያስረዳል ንባቤን ከጨረስኩኝ በኋላ ያንን ከፍል ከአንደገና በአንከሮ ለማጤን ወሰንኩኝ ብዙዎቹን የማከዱዌልን ሙግቶች በቂ ሆነው አላገኘኋቸውም አርሱ ከግምት ያልከተታቸው ሌሎች አማራጭ ትንታኔዎች ነበሩ ለምሳሌ ያህል ጴጥሮስ ኢየሱስን የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ብሎ የጠራበትን ማቴዎስ የኢየሱስን አምላከነት ለማሳየት ይጠቅሳል ነገር ግን ለዚህ ምላሽ የሚሆን ሙግት ገና ከልጅነቴ ተምሬያለሁ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አዳም ሰለሞንና ስማቸው ያልተጠቀሰ ግለሰቦች ሳይቀሩ ብዙ ሰዎች የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው ተጠርተዋል መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጆች መሆን እንደምንቸል ከመናገር አልፎ ሰዎችን አማልከት ብሎ የሚጠራባቸው ቦታዎች አሉ የሆነ ቦታ ላይ ደግሞ ኢየሱስ በሁሉ ቦታ መገኘትን የመሳሰሉት የአምላከ ባሕርያት እንዳሉት ለማስረዳት ማከዱዌል ማቴዎስና ሉቃስን ይጠቅሳል ነገር ግን አንዳቸውም የሚያሳምኑኝ አልነበሩምሁሉም ከፍሎች የሚናገሩት ኢየሱስ ተዓምራትን ማድረጉን ነው ነገር ግን ሙስሊሞች ለኢየሱስ ተዓምራት የሚሰጡት ማብራርያ በጣም ቀላል ነው በኢየሱስ ኃይል ሳይሆን በአላህ ፈቃድ የተደረጉ ናቸው ቁርአን የሚያስተምረው እርሱን ሲሆን ኢየሱስ ያደረጋቸው ተዓምራት ከአብ መሆናቸውንና ከራሱ አንዳች ማድረግ እንደማይችል የተናገረባቸውን የመጽሐፍ ቅዱስ ከፍሎች ገና ድሮ በቃል በመሸምደድ ይዣቸዋለሁከርስትናን ለመቃወም እንደሰለጠነ ሙስሊም በማከዱዌል ንግግሮች ውስጥ ምንም አዲስ ነገር አላገኘሁም እነዚህን ሙግቶች ደግሞ ወደ ከርስቲያኖች የመመለስ ስልጠናዎችን ወስጃለሁ ነገር ግን በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ የሚገኙ የኢየሱስን አምላከነት ለመቃወም መጠቀም የምቸላቸው ጥቅሶች ቢኖሩም ኢየሱስ አምላከ መሆኑን በግልፅ የሚያሳዩ ሌሎች ጥቅሶች ደግሞ መኖራቸውን አንድቀበል በማድረግ ረገድ ማከዱዌል ተሳከቶለታልለምሳሌ ያህል ሰዎች ሁሉ አብን እንደሚያከብሩት ወልድን ያከብሩ ዘንድ በማለት ኢየሱስ ተናግሯልኞ በተጨማሪም ኢየሱስን አምላኬ ብሎ የጠራው ደቀ መዝሙር በኢየሱስ አድናቆት ተችሮታልችእነዚህን ጥቅሶች ከዚህ ቀደም ያልሰማኋቸው ሲሆን ከእኔ አስተሳሰብ ጋር የሚሄዱ አልነበሩም ሊሄዱም አይችሉም ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች የሚናገርበት ወይም የሚፈቅድበት ምንም ዓይነት መንገድ የለም ቢያን እኔ የማውቀው ኢየሱስ ይህንን ሊያደርግ አይትልም እነዚህን ጥቅሶች ልጅ ሆፔ ከሸመደድኳቸው ተቃራኒውን ከሚናገሩት ጥቅሶች ጋር ለማጣጣም በአአምሮዬ ውስጥ ማውጣትና ማውረድ ጀመርኩኝ እንዴት ነው አንድ ላይ ሊገጥሙ የሚችሉት። መሐመድ ቁርአንን በሃያ ሦስት ዓመታት ውስጥ ለጻሐፍቱ እየነገረ እንዲጽፉለት ያደርግ ነበር ቁርአን በአንድ ጥራዝ የተሰበሰበው ከአርሱ ሞት በኋላ ነበር ከአሥርተ ዓመታት በኋላ የተነገሩ ጥቅሶች ብዙ ጊዜ በመካከላቸው ምንም መያያዝ በሌለበት ሁኔታ ተከታትለው ይቀመጣሉ በዚህም ሳብያ ሙስሊሞች ቁርአንን ሲተረጉሙ በዙርያው ላሉ ሌሎች ጥቅሶች የሚሰጡት ትኩረት አናሳ ነው አውዱን ለማወቅ አስባብአን ኑዙል በመባል የሚታወቁ ማብራሪያዎችን ወይም ሐዲሶችን ይጠቀማሉ የቁርአን ታሪኮች ቁርጥራጭ ከመሆናቸው የተነሳ መጀመርያ መካከልና መደምደምያ ያለው አንድ ታሪከ ብቻ ነው የዮሴፍ ታሪከ የተቀሩት ሌሎች ትረካዎች ሁሉ ከመካከል ይጀምራሉ ወይም ጀምረው እስከ መጨረሻው ድረስ አይዘልቁም ቁርአንን ለመረዳት ወደ አስተማሪዎቼ ለመሄድ መገደዴ የሚያስገርም አይደለም ነገር ግን ከማከዱዌል መጽሐፍ ጋር አያይዝፔ መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ውስጥ በመግባት ሳነብ ወንጌላት ግልፅ የሆኑ አውዶች ያሏቸውና ወጥነት ያላቸው ታሪኮችን እንደሚያቀርቡ ተገነዘብኩኝ አስባብአጉኑዙል የቁርአን አናቅፅ የወረዱበትን አውድ ወንጌላትን ለመረዳት ምንም ዓይነት ማብራሪያዎች በጥልቀት የሚዘግብ አያስፈልጉምማንኛውም ሰው መጽሐፍ ቅዱስን የእስልምና ጽሑፍ ስብስብ አንብቦ መረዳ ይትላል ቁርአንን ስናነብ እንደምናደርገው የሆነ ሐሳብ ለመግለፅ በአንድ የወንጌል ጥቅስ ላይ ብቻ አንንጠለጠልም ወንጌሉን በሙሉ በማንበብ የጸሐፊውን ዓላማና ግብ በመረዳት መጽሐፉ ለራሱ እንዲናገር መፍቀድ ይኖርብኛል በዚህ አዲስ መረዳት ታጥቄ የዮሐንስን ወንጌል ለመተርጎም ከመሞከሬ በፊት እስከ መጨረሻው ማንበብ እንዳለብኝ ወሰንኩኝ መሬት ላይ ተቀምጩ የአባን መጽሐፍ ቅዱስ ዮሐንስ አንድ ላይ ገልጩ ማንበብ ጀመርኩኝ ያገኘሁት ነገር ምቾት የሚሰጠኝ አልነበረም በመጀመሪያው ቃል ነበረ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ ቃልም አግዚአብሔር ነበረፈ ይህ በመጀመሪያው በአግዚአብሔር ዘንድ ነበረ ሁሉ በአርሱ ሆነ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም በጣም ግልፅ ነው አራት ነጥብ አነዚህን ጥቅሶች ደግሜ ደጋግሜ በማንበብ አሰላሰልኳቸው ሌላ ምንም ዓይት አማራጭ ትርጉም የለም እነዚህ ጥቅሶች የሚናገሩት እግዚአብሔር ዓለምን በቃሉ እንደፈጠረ ቃል ከአግዚአብሔር ጋር በዘላለማዊነት ይኖር እንደነበረ ራሱ እግዚአብሔር እንደሆነና ነገር ግን ደግሞ በተወሰነ ሁኔታ ከእርሱ የተለየ እንደሆነ ነው ቃል ኢየሱስ መሆኑ ግልፅ ነው ይህንን የተረዳሁት ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ እንደርሱ ስለሚል ብቻ ሳይሆን ቁርአን ራሱ አላህ ቃል ብሎ ስለሚጠራው ነው ከዚህ በተጓዳኝ ቁጥር ለጥርጣሬ የሚሆን ምንም ዓይነት ቦታ አይሰጥም ቃልም ሥጋ ሆነ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ከብር የሆነው ከብሩን እየን የግድ ኢየሱስ መሆን አለበት ግራ ከመጋባቴ የተነሳ ቃሉን አያሰላሰልኩኝ መጽሐፍ ቅዱሱን አስቀምጩ በከፍሉ ውስጥ ወዲያ ወዲህ መንቀሳቀስ ጀመርኩኝ ይህ የዮሐንስ የመጀመርያው ምዕራፍ ነው የመጽሐፉ መግቢያ ነው በዘመናዊ መጻሕፍት ውስጥ እንደሚገኙት መግቢያዎች የተቀረውን የመጽሐፉን ከፍል የምናነብበትን መነፅር ይሰጠናልዮሐንስ መጽሐፉን ስታነቡ ሳላችሁ ኢየሱስ ከአብ ጋር አብሮ ዘላለማዊ የሆነና በመፍጠር ሂደትም ተባባሪው እንደነበር አስታውሱ የሚል ይመስላል በሌሎቹ የወንጌሉ ከፍል ውስጥ የሚገኙትን ውጥረቶች ለማስታረቅ የምችልበት አውድ ይህ ነው ጥቅሶችን ሳስታርቅ ምንም ዓይነት ችግር ቢገጥመኝ የዮሐንስን የመግቢያ ቃል ማስታወስ ያስፈልገኛል ኢየሱስ አምላክ ነው ከዚህ እውነት ላመልጥ የምችልበት ምንም ዓይነት መንገድ አለመኖሩን ስገነዘብ ወዲያ ወዲህ መሄዴን አቁሜ የተገለጠውን መጽሐፍ ቅዱስ ፍጥጥ ብዬ ተመለከትኩት አሁንም ዮሐንስ ላይ ተከፍቷል ማመን ተስኖኛል እውነት ሊሆን አይቸልም ኢየሱስ አምላከ ሊሆን አይችልም የሆነ ማብራርያ መኖር አለበት አለበለዚያ ተታልያለሁ የሆነ ማብራርያ መኖር አለበት አለበለዚያ ቤተሰቤም ሆነ የምወዳቸው ወገኖቼ ሁሉ በውሸት ወጥመድ ውስጥ ገብተዋል ኢየሱስ በእውነት አምላከ መሆኑን ከተናገረ ቁርአን ተሳስቷል እስልምናም የውሸት ሃይማኖት ይሆናል የሆነ ማብራርያ መኖር አለበት ያ ማብራርያ ምን እንደሆነ አላውቅም ነገር ግን ብቻ መኖር አለበት ስለመኖሩ ምንም ጥርጣሬ አልነበረኝም አላህ ደግሞ አንደሚያሳየኝ ተስፋ ነበረኝ የጋራ ጸሎት ወደምንጸልይበት ከፍላችን ፈጠን ብዬ ሄድኩኝ ወደ መጸለያው ቦታ ከደረስኩኝ በኋላ አጆቼን ወደ ጆሮቼ አንስቼ አላሁ አከበር ካልኩኝ በኋላ የነፍስል ጸሎት ሁለት ረካዎችን ። የዮሐንስን ወንጌል አጥንቼ ልምጣ ነገር ግን ሌላ መጽሐፍ እስጥህና አስተያየትህን ትነግረኛለህ ጥሩ ይመስላል ነገር ግን ዕና ያቂፀ ከሚለው መጽሐፍ የተሻለ ሥራ ይጠበቅብሃል ዳዊት በሚቀጥለው ጊዜ ተለቅ ያለ መጽሐፍ ብታመጣልኝስ ዳዊት ሳቀ እንደጠየከው ይሆንልሃል ከጥቂት ቀናት በኋላ መጠኑ ትልቅ የሆነ መጽሐፍ ይዝ በአባ ከፍል ውስጥ በሆዴ ተኝቻለሁ የመጽሐፉ ርዕስ ፍርድ ዖሟሻ ማኃረኛ ይላል በጆሽ ማከዱዌል የተጻፈ ቢሆንም ነገር ግን ደረጃው ከፍ ያለ ነበር ጆሽ ማከዱዌል ስለ ከርስትና ምንጮች ባጠናባቸው ረጅም ዓመታት ውስጥ ያሰባሰባቸው ማስታወሻዎች የተጠራቀመበት ወደ ስምንት መቶ ገፅ የሚረዝም ጥራዝ ነበር ምንም የስጋት ስሜት አላደረብኝም ነበር የዮሐንስንወንጌል በተመለከተ በቅርቡ በዳዊት ላይ ያገኘሁት ድል ድፍረትን አጎናፅፎኛል አላህ ከጎኔ መሆኑ ከመቸውም ጊዜ በላይ ይሰማኛል በአርሱ ላይ የሚነገር የትኛውም ተቃውሞ ሊፀና እንደማይችልና የኢየሱስ አምላከነት በኋለኛው ዘመን ወደ ከርስትና የተጨመረ ስለመሆኑ በጣም እርግጠኛ ነበርኩኝ ኢየሱስ አምላከ መሆኑን ተናግሮ ከሆነ ግልፅ የሆነውን ንግግሩን በኋለኛው ወንጌል ውስጥ ብቻ ሳይሆን በቀደሙት ወንጌላትም ውስጥ ማግኘት ይኖርብናል ኢየሱስ አምላከ መሆኑን ስለመናገሩ በማርቆስ ወንጌል ውስጥ ተጽፎ ማየት ያስፈልገኛል ሳላቅማማ ስለ ኢየሱስ አምላከነት የሚናገረውን ከፍል ፈጠን ብዬ በመከፈት ንባቤን ጀመርኩኝ ማከዱዌል አእምሮዬን ያነበበው ይመስል ከጅምሩ በማርቆስ ወንጌል ውስጥ የሚገኝ ኢየሱስ ስለ ራሱ የሰጠው ሕጋዊ ምስከርነት ብሎ ጽፏል አርሱ ከርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ስለመሆኑ ሊቃ ካህኑ በጠየቀው ጊዜ እኔ ነኝ የሰው ልጅም በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ በሰማይም ደመና ሲመጣ ታያላችሁ በማለት ነበር የመለሰው እኔ ነኝ ከሚለው ውጪ ይህ ንግግር ብዙም ግልፅ አልሆነልኝም ነበር ማከዱዌል ለምን አንደ ዋና የሙግት ሐሳብ እንዳቀረበውም ቶሎ አልተከሰተልኝም ነበር ኢየሱስ ይህንን ሲል ምን ለማለት ፈልጎ ይሆን። ቢል አሁንም ከፋዩ አንድ ተራ ሰው አለመሆኑን ከግንዛቤ አላስገባህም ይህ እግዚአብሔር ነው ይህ የትሪሊዮን ዶላሮችን ዕዳ በአንድ ዶላር እንደ መከፈል አይደለም ይህ የትሪሊዮን ዶላሮችን ዕዳ ከቁጥር በላይ በሆነ የባንክ መዝገብ እንደ መከፈል ነው የአግዚአብሔር ሕይወት በአፅናፈ ዓለም ውስጥ ከሚገኙት ሕይወቶች ሁሉ ድምር ይልቅ ዋጋ አለው የእርሱ ሞት እኛ ሁላችን ልንሞት ከተገባን በላይ የሞት ዕዳችንን ይከፍላል ድጋፍ እንደሚሰጠኝ ተስፋ በማድረግ ዛከን ዞር ብዬ ተመለከትኩት የመመለስ ኃላፊነት ያንተ ነው እንደማለት ዕይታዬን በዕይታ መለሰው ሐሳቤን ከእንደገና ሰደርኩ መልካም ዳዊት ሌላ አንድ ችግር አለ ይህንን ሁሉ ስትናገር አንድ ሰው ኃጢአት በሠራ ቁጥር መሞት አለበት የሚል ቅድመ ግንዛቤ በመያዝ ነው ይህን መቼም ልቀበለው የምቸለው አይደለም ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ነው ሮሜ ዳዊት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን ሲጠቅስ ሁል ጊዜ ያስደንቀኛል ደግሞም ያበሳጨኛል እስላማዊ አስተምህሮዎችን የሚደግፉ ጥቅሶን መጥቀስ የምችለው አልፎ አልፎ ብቻ ነው ምክንያቱም አብዛኛውን ነገር የተማርኩት ከአስተማሪዎቼ ነውና እነርሱ ራሳቸውም ቢሆኑ ጥቅሶቹን አያውቋቸውም በዚህ ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስን መጥቀሱ ልዩነታችንን አከረረው ውነቱን ለመናገር መጽሐፍ ቅዱስ አንደርሱ ማለቱ ምንም ግድ አይሰጠኝም ምንም ትርጉም የሚሰጥ አይደለም ትንሹን ስህተት ከትልቁ ወንጀል እኩል የሚቀጣ ምን ዓይነት ዳኛ ነው። ሙግት ለእስልምና በመሐመድ ወይም በቁርአን ልትጀምር ትችላለህ ከዚያ ቀጣዩ ነገር ምን እንደሚሆን አብረን እናያለን ማይከ ቅር እንደማይለው እርግጠኛ ነኝ ስለ ቡዲሂዝም ተነጋግረን ስለጨረስን አዲስ ርዕስ እየፈለግን ነው ስለ ጉዳዩ ባሰብኩኝ ቁጥር እየወደድኩት መጣሁ ለዳዋ እንደሚሆን አጋጣሚ ነበር የቆጠርኩት ስለ ከርስትና ስለማናወራ ከአባቴ ጋር ስለ ከርስቶስ ስቅለት ስንነጋገር ከነበረው ሁኔታ በተፃራሪ ውይይቱን እኔ አንደምቆጣጠረው አሰብኩኝ በእርግጠኝነት እንደርሱ አደርጋለሁ በሚቀጥለው ጊዜ ስለ መሐመድ በመነጋገር እንጀምርና ከዚያ ወደ ቁርአን አልፋለሁ ዳዊት የቀን መቁጠርያውን ከተመለከተ በኋላ ቀጣዩ የስብሰባ ጊዜ ከሁለት ሳምንታት በኋላ መሆኑን አረጋገጠ አቅዳችንን መልከ ካስያዝን በኋላ ያቺን ዕለት መጠባበቅ ጀመርን ነገር ግን ሁላችንም የየራሳችን ፍላጎት ነበረን ለዚያች አለት ዝግጅት ሳደርግ ከአንዱ የሕይወት ምዕራፍ ወደ ሌላው ለማለፍ ጫፍ ላይ መድረሴ አልታወቀኝም ነበር በወላጆቼ የተገነባልኝን ዓለም በፀጋ ተቀበዬ ነበር ይህ ዓለም እስልምና ላይ ምንም ዓይነት ጥያቄ የማይቀርብበት ዓለም ቢሆንም ከፊቴ የነበረው ጊዜ የቆምኩበት መሠረት በሚገባ ተፈትሾ የሚፈራርስበት ነበር ሪገርም ዱም ሶው ማፇ ጽ ያግራንድዮ ራጄሮዕ ሟፇጀጋ ዖሯይማድፎፖዊ ፖናሦኖ ሥረፖፓ ዳፀሪያፖረ ፈፆሆኑ ፀገርጳታ መዳጓጋፍ ምና መማፖፎ ያደራፈ ናምው ጎቶፖው ያዳፉታ ይቲቅ ዳዕሥዎሥሰፅማጃሃ ርከከእ እከ ይያቻፓ ከፍል ከበ ዉከመቿ ከጡነተሻጡ ነገር መፅመድ ያጋ መሳሪ ታመፖሁ ያምመያሰረው ዕው ምዕራፍ ሠላሳ ስድስት መሐመድን በአጉሊ መነፅር የእስልምና መልዕከት ከመልዕከተኛው ጋር የተቆራኘ ነው ለአንዱ መታመን ለሌላው መታመን ነው አንዱ በሌላው ይተረጎማል ይህንን ጉዳይ አስገራሚ የሚያደርገው ደግሞ ስለ አላህ ያለው እውነታ ተመሳሳይ አለመሆኑ ነው የሙስሊሙ ማሕበረሰብ በአላህ ላይ ጥያቄ የሚያነሱትን ሙስሊሞች ብዙ ጊዜ ይታገሳቸዋል ነገር ግን በመሐመድ ላይ ጥያቄ ማንሳት ከማሕበረሰቡ መገለልን ያስከትላል የከፋ ነገርም ሊከተል ይቸችላል መሐመድ ሰው መሆኑንና እንደማንኛውም ሰው ስህተት የሚሠራ መሆኑን እያንዳንዱ ሙስሊም ያለማቅማማት ቢቀበልም ነገር ግን እንከን አልባ እንደሆነ ሰው የመቁጠር ሁኔታም ይታያል እስላማዊ ሥነ መለኮት ለመሐመድ ለልፈ ጎ ሟሰሐ ፍፅምና ላይ የደረሰ ሰው የሚል መዕርግ እስከማጎናፀፍ የተለጠጠ ነው ነገር ግን ወደ ሙስሊሞች ልብ እጅግ ከመቅረብ አልፎ መሐመድ እአስልምናን በሁለንተናው የሚገልፅ ነው የመላው እስላማዊ ሥልጣኔ ሰንደቅ ነው በሐዲስና ትውፊቶች ምከንያት የሙስሊም ሃይማኖት ባሕልቅርሶችና መለያዎች ሁሉ ምሉዕ የሚሆኑት በመሐመድ ነው ለዚህ ነው ሙስሊሞች በእርሱ ላይ የሚሰነዘሩትን ጥቃቶች ሁሉ በእነርሱና የእነርሱ በሆነው ነገር ሁሉ ላይ እንደተሰነዘሩ ጥቃቶች የሚቆጥሩት ለዚህ ነው በደምሳሳው ስንናገር ሙስሊሞች በትዕግስት ስለ መሐመድ መወያየት የሚሳናቸው ከርዕሱ ጋር ያልተገናኙ ዝባዝንኬ ነገሮችን ወደ ውይይቱ ያመጣሉ ስለ መሐመድ ከተነሳ ለዘመዶቻችን ታማኞች ስለመሆንና የእስራኤልና ፍልስጥኤም ግጭቶችን የመሳሰሉ ወቅታዊ ጉዳዮችን እንኳ ወደ ውይይቱ ሊያመጡ ይትላሉ ከዚህ የተነሳ በማይከ መኖርያ ቤት ውስጥ ስለ መሐመድ ውይይት ባደረግንበት ወቅት ፍላጎቴን በጥልቀት መረዳት የቻለ ሰው አልነበረም መሐመድን በጥሩ ሁኔታ አሳምሮ በማቅረብ እስልምናን ከፍ ከፍ የማድረግ ተስፋ ስለነበረኝ በጉጉት ተሞልቼ ነበር ሌሎች ታዳሚያን ደግሞ ለመማርና እኔ የምናገረውን ነገር በአንከሮ ለማጤን ነበር በቦታው የተገኙት ጥያቄዎቻቸው በእኔ ላይ የሚፈጥሩትን ተፅዕኖ ቢያስተውሉ ኖሮ የበለጠ የተለሳለሰ ንግግር በተጠቀሙ ነበር ስሜቴን ማወቅ ባለመቻላቸው ደስተኛ ነበርኩኝ የስብስቡ ስብጥር ካሰብኩት በላይ ነበር ማይከ ዳዊትና ጥቂት ከርስቲያኖች ነበሩ ዛከ ቡድሂዝምን በመወከል ተገኝቷል ነገር ግን ደግሞ አምላክ የለሾችና ስለ አምላከ መኖር እርግጠኞች መሆን እንደማይችሉ የሚያምኑ ወገኖችም በቦታው ተገኝተዋል እነዚህ ወገኖች አንዱ መርማሪ ፖሊስ ሌላው አስትሮ ፊዚሲስትና ሁለቱ መምህራን ነበሩ የመግቢያ ንግግሮች ከተደረጉ በኋላ መድረኩ ተለቀቀልኝ ስለ መሐመድ ለመሟገት ገላጭ ምስሎችንና ቻርቶችን የተጠቀምኩ ሲሆን ከልጅነቴ ጀምሮ የተማርኳቸውን መረጃዎች ነበር ያካፈልኩት በምዕራብ የሚኖሩት ሙስሊሞች ድልድይ ለማበጀትና ወደ አስልምና የሚመጡትን ሰዎች ለማጥመድ የሚጠቀሙትን ዘዴ በመጠቀም እስልምናንና አስላማዊ ታሪኮችን የማቅረብ ሙከራ አደረኩኝ ከ የሸብር ጥቃት ወዲህ ከነውጠኛ እስላማዊ ገፅታ በተቻለ መጠን ራስን ማራቅ በምዕራብ የሚኖሩት ሙስሊሞች ጭንቀት ሆኗል እኔ ደግሞ የአሕመዲ ሙስሊም እንደመሆኔ መጠን ይህ ለኔ እጅግ አስፈላጊ ነበር እስልምና ሰላማዊ ሃይማኖት መሆኑንና መሐመድም ደግሞ በሰው ልጆች ታሪከ ከተነሱት ሰዎች ሁሉ እጅግ ርህሩህና ደግ ሰው መሆኑን በመናገር ሙማሣቴን ጀመርኩኝ በዓለም የንግድ ማዕከልና በፔንታገን ላይ የተፈፀሙት ጥቃቶች እስልምናን እንደማይወከሉ ለሁሉም ሰው በአፅንዖት አረጋገጥኩኝ መስከረም ዝ አውሮፕላኖቹን የጠለፉት ሽብርተኞች አስልምናንም ጭምር ጠልፈዋል የሚል አባባል ጠቀስኩኝ ይህ አባባል የራሴ ሳይሆን አንድ የመስጊድ ኢማም ሲናገር የሰማሁት ነበር ኢስላም የሚለው የአረብኛ ቃል ሰላም ከሚለው ጋር ተመሳሳይ ከሆነ ሥረወ ቃል የመጣ መሆኑንና የመሐመድም ሕይወት ይህንኑ እንደሚያንፀባርቅ አብራራሁኝ መካውያውን ሙስሊሞች ላይ ካደረሱት በደል በተፃራሪ መሐመድ መካን ባሸነፈበት ፅለት ያሳየውን ምህረት የሚያወሳውን ታሪከ ጠቀስኩኝ መሐመድ የተሳተፈባቸውን ሌሎች ሰልፎች ሁሉ በመጥቀስ ሁሉም የመከላከል ጦርነቶች እንደነበሩ አላህ ደግሞ ተዓምራዊ በሆነ መንገድ ጣልቃ በመግባት ማፅደቁን በአፅንዖት ተናገርኩኝ ከዚህ በተጓዳኝ መሐመድ ስለ ሳይንስ የነበረውን የጠለቀ ግንዛቤ አስረዳሁኝ በሙስሊም ዓቃቤያነ እምነት ዘንድ ይህ የተለመደ ነው መሐመድ ስለ ሽል ዕድገት ስለ ሥነ ፈለከና ስለ ጂኦሎጂ ዕውቀት አንደነበረውና አላህ ካልገለጠለት በስተቀር ይህንን ዕውቀት ማግኘት እንደማይችል ተሟገትኩኝ ይህም ደግሞ መሐመድ በአላህ የተባረከ እውነተኛ ነቢይ መሆኑን አንደሚያመሰክከት ተናገርኩኝ ሌላው ሙስሊም ዓቃቤ እምነታውያን የሚጠቀሙት ስልት ለአስላማዊ ሙግቶቻቸው ድጋፍ ለማግኘት መጽሐፍ ቅዱስን መጥቀስና እስልምና የአዲስ ኪዳን እንዲሁም የብሉይ ኪዳን ምልዓት መሆኑን ማስረዳት ነው ይህንን ለማድረግ ስለ መሐመድ የተነገሩ ትንቢቶች አንደሆኑ ያሰብኳቸውን ሁለት ጥቅሶች አንዱን ከብሉይ ሌላውን ከአዲስ ኪዳን ጠቀስኩኝ የመጀመርያው ዘጸአት ሲሆን እንደ ሙሴ ያለ ነቢይ እንደሚነሳ ይናገራል ኢየሱስ በሁሉም ረገድ እንደ ሙሴ ባለመሆኑ ይህ የግድ መሐመድ መሆን እንዳለበት ተሟገትኩኝ ከዚያም ዮሐንስ በመጥቀስ ኢየሱስ ሰዎችን ወደ እውነት የሚመራ አፅናኝ ከእርሱ በኋላ እንደሚመጣ መናገሩን አስገነዘብኩኝ ከኢየሱስ በኋላ ትልቅ የሚባል የሃይማኖት መሪ ከመሐመድ ሌላ ስላልተነሳ ይህ ሰው መሐመድ መሆን አለበት አልኩኝ አስልምና የመጨረሻ መልዕከት መሆኑን መሐመድም አይሁዳዊነትንና ከርስትናን ለመሻር ሳይሆን ለማፅናትና ወደ አንዱ አውነተኛው አምላከ ከአንደገና ለመመለስ መምጣቱን በመናገር ሙግቴን አጠናከርኩኝ የመሐመድ መልዕከት ዓይን ስለ ዓይን የሚለውን የሙሴን ፍትሃዊ ሕግና ሌላኛውን ጉንጭህን አዙረህ ስጠው የሚለውን የኢየሱስ የምህረት መልዕከት በማጣመር ዋና መመርያ ያደረገ መሆኑን እንዲሁም እስልምና ለሰው ልጆች የተላከ የመጨረሻው መልዕከት መሆኑን አፀናሁኝ ይህንን የመደምደምያ መልዕከቴን ስናገር ሙስሊሞች የሚያመልኩት አምላከና አይሁዶች እንዲሁም ከርስቲያኖች የሚያመልኩት አምላከ አንድ ዓይነት መሆኑን በማረጋገጥ ነበር ለአርባ አምስት ደቂቃዎች ያህል የተናገርኩኝ ሲሆን እስልምናን በትከከል ማሳየቴንና የመሐመድን ነቢይነት የሚያረጋግጥ ሙግት በመንፈሳዊ ቅንዓት በተሞላ ሁኔታ ማቅረቤን እርግጠኛ ነበርኩኝ ነገር ግን ጥያቄዎች መነሳት ጀመሩ ከርስቲያኖችን ስለ ሥላሴ እጠይቅ እንደነበሩት ዓይነት ጥያቄዎች ሁሉ ከቅንነት የመነጩ የማብራርያ ጥያቄዎች ነበሩ ነገር ግን ለመጀመርያ ጊዜ ጥያቄ ተቀባይ ሆፔ ራሴን አገኘሁት ማይከ ጀመረ ቢል ጥያቄ አለኝ አስልምና በሰይፍ መስፋፋቱን ሰምቻለሁ አንተ ግን መሐመድ ራስን በመከላከል ጦርነቶች ብቻ እንደተሳተፈ ነው የነገርከን ያንተ አመለካከት ትክከል መሆኑን በማስረጃ ልታረጋግጥልኝ ትችላለሁ። በማለት ጠየቀኝ ጥርጣሬን አእንደማያጭር በደፈናው መለስኩለት መሐመድ ከአይሻ ጋር የፈፀመውን ጋብቻ በተመለከተ እንዲሁ ዳዊት ተቃውሞውን አቀረበ በብዙ ሐዲሳት መሠረት መሐመድ ሲያገባት ስድስት ዓመቷ ነበር ጋብቻውን ደግሞ ሲያሟላ ዘጠኝ ዓመቷ ነበር በዚያን ጊዜ ዕድሜው ሃምሳ ሁለት ነበር በእርሱ ምሳሌነት ምከንያት በሙስሊሙ ዓለም ውስጥ የሚገኙ ሴቶች ለደህንነታቸው አደገኛ በሆነ ዕድሜ ላይ ለማግባት አየተገደዱ መሆናቸውን ገለፀ ነገር ግን የኔ ጀማት እነዚህ ሐዲሳት ትከክል እንዳልሆኑ ስለሚያስተምር ጉዳዩ አምብዛም አሳስጨነቀኝም ዳዊት የመሐመድን ነቢይነት የሚቃወሙ ትውፊቶችን አንድ በአንድ አቀረበልኝ ከብደታቸው ደግሞ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚጨምር ነበር መሐመድ በመርዝ ጉዳት ደርሶበታል በሞቱ አልጋ ላይ ሆኖ እያጣጣረ በመርዙ ምከንያት እየሞተ አንደሆነ ተሰምቶት ነበር አስማት ተደርጎበት ነበርሞ ኋላ ላይ ከሰይጣን አንደሆኑ የተናገራቸውን መገለጦች አምጥቶ ነበር ለገንዘብ ብሎ ሰዎችን አሰቃይቷል ባልታጠቁ አይሁዶች ላይ ጥቃት ፈፅሟል የማደጎ ልጁ ሚስት የሆነችውን ዘይነብን ለማግባት ሲል ትዳሯን አፍርሷል ሰዎች የግመል ሽንት አንዲጠጡ አዚል ይህ ዝርዝር ማቆምያ የለውም መጀመርያ ለእነዚህ ሐዲሳት አንድ በአንድ መልስ ለመስጠት ሞከሬ ነበር ነገር ግን እንደርሱ ማድረጌን በቀጠልኩኝ ቁጥር ሚዛናዊ አለመሆኔ አየገባኝ መጣ የምወደውን ነቢይ የመሐመድን ታሪከ የሚያጎድፉ ሐዲሳትን አንዴት ማጣጣል እንደምችልና ስብዕናውን የሚያልቁ ሐዲሳትን እንዴት ማፅደቅ እንደምችል ለማወቅ ዕውቅ በሆኑ ሊቃውንት ስለ ሐዲስ ሥነጥናት የሚያስተምሩ መጻሕፍትን ማጥናት ምሑራዊ የሆኑ ትምህርቶችን መስማት የተለያዩ ማብራርያዎችን ማንበብ ጀመርኩኝ ነገርግን ሁለቱን የማላቅቅበትን መቁረጫ ማግኘት ተሳነኝ መሐመድ የግድ ነቢይ መሆን ስላለበት እነዚህ ታሪኮች ውሸት መሆን አለባቸው ከሚለው ጭፍን አስተሳሰብ ውጪ ምንም ነገር ላገኝ አልቻልኩኝም ነገር ግን ከተከበሩ ምንጮች የተገኙ ጉልቁ መሣፍርት የሌላቸው ታሪኮች ነበሩ ጊዜ በሄደ ቁጥር ትከከለኛነታቸውን የካድኳቸው ሐዲሳት ከልክ አለፉ ማድረግ የምችለው አርሱን ነበር እንደርሱ ካላደረኩኝ እሰጥማለሁ የግለ ታሪከ ጸሐፍትና አስተማሪዎቹ ለምን እንደዚህ ዓይነት ነገር እንደሚፈፅሙ እየገባኝ መጣ ወደ መቶ የሚጠጉ እንደዚህ ዓይነት ታሪኮችን መካዴን ስረዳ መራራውን ሃቅ ለመቀበል ተገደድኩኝ እነዚህ ታሪኮች የተገኙት የእስልምናን ታሪካዊ መሠረት ከገነቡት ምንጮች ነው መሠረቱ ሳይናጋ ስንቱን መካድ እችል ይሆን በሌላ አነጋገር የትውፊቶቹን ትከክለኛነት መካዴን ከቀጠልኩኝ ሲጀመር አርሱን ነቢይ ብዬ የምጠራበት መሠረት የለኝም ማለት ነው መሐመድን ሊዋጅ የሚችል አንድ ነገር ከሌለ ከታሪክ ያለፈ አንድ ነገር ከሌለ በስተቀር ሸሃዳን የምመሰከርበት ምንም ዓይነት መንገድ አይኖረኝም ከዚህ አጣብቂኝ ለመውጣት መንገዱ አንድ ብቻ ነው ቁርአን ዶሂ። ቋው ያንፖታ መድፍ ታጋያ ምዕራፍ አርባ የቁርአን ሙግት እስኪ ስለ ፈጣሪ ሚስጢርና ጥበብ ስለ ኃይሉ ታላቅነት ስለ ፍፅምናው ስለ መለኮታዊ ተስፋዎቹና ትንቢቶቹ ለማሰብ ሞከሩ እነዚህ ሁሉ ቁሳዊ በሆነ መጽሐፍ ገፆች ውስጥ ሰፍረው መጽሐፉን የፈጣሪ ባሕሪ ተካፋይ ማድረጋቸውን ስታስቡ ሙስሊሞች ለምን ለቁርአን ከፍተኛ ከብር አንደሚሰጡ ትረዳላችሁ ቁርአን ለእስልምና ልከ እንደ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሆነ መታሰብ የለበትም እንደርሱ አይደለም ለሙስሊሞች ቁርአን ወደ አላህ ተሠግዎ የቀረበ ነገር ነው የእስልምናንም እውነተኛነት ለመግለጥ የሚያቀርቡት ማስረጃ ነው በከርስትና ውስጥ የሚገኝ የተሻለ ንፅፅር የኢየሱስ ተሠግዎና ትንሣኤ ነው ቁርአን ለአስልምና ሥነ መለኮት የዚያን ያህል ማዕከላዊ ነገር ነው የእምነቴ መሠረት ይህ ነው እንደ ሁለተኛ የዕምነቴ አዕማድ የምቆጥረው መሐመድ የትከከለኛነቱ ማረጋገጫ በቁርአን ላይ የተመሠረተ ነው ይህንን ቅዱስ መጽሐፍ መመርመር ስጀመር በፍርሃትና በአከብሮት ነበር የእስልምና እውነተኛነት መሐመድ የቆመለት ዓላማ ሁሉና የኔም ሕይወት ጭምር የተመሠረተው በቁርአን መለኮታዊ መገለጥ ላይ ነው የመሐመድን ሕይወት መመርመር ስጀምር እንደነበረው ሁሉ ቁርአንም ምርመራውን ማለፍ ይቸላል የሚል ግምት ነበረኝ ከኡማ አባላት መካከል አንድም ሰው መለኮታዊ መገለጥ መሆኑን የሚጠራጠር የለም ቁርአን ፍፁምና ተዓምራዊ መሆኑን ምዕራባውያን ሊቃውንትን ጨምሮ ማንም አጠያያቂ ማድረግ እንደማይቸል እርግጠኞች ነን ሙግታችን እጅግ ጠንካራ መሆኑን እናምናለን ስለ ቁርአን መለኮታዊነት ጎልቶ የሚነገረው ሙግት ማንም እርሱን የሚመስል ጽሑፍ መፍጠር አለመቻሉ ማለትም አስደናቂ አጻጻፉ ነው ማንም የእርሱን ጥዑመ ልሳን መፍጠር አይቸልም እንላለን ሙግታችን ከራሱ ከቁርአን የተገኘ ነው በመሐመድ ዘመን የነበሩት ሰዎች ቁርአን የራሱ ፈጠራ መሆኑን በመናገር ሲከሱት ተጠራጣሪዎች እርሱን የሚመስል ጽሑፍ እንዲፈጥሩ በተደጋጋሚ ሲጠይቃቸው እናያለን ከሰዎችም ከጂኒዎችም ጋር በማበር ቢሞከሩ እንኳ አይሳካላቸውም የቁርአን ግድድር ይህንን ይመስላል ማንም ሰው ከእርሱ ጋር ሊፎካከር የሚችል ጽሑፍ መጻፍ አይችልም ከልጅነታችን ጀምሮ እነዚህን ተግዳሮቶች በቁርአን ውስጥ እያነበብን እንደ ማደጋችን መጠን እንዲሁም የምንከተለው ንፅረተ ዓለም ቁርአን እጅግ ውብ መሆኑን በሚሰብኩ መምህራን የተቃኘ አንደመሆኑ መጠን እኔና እኔን መሰል ሙስሊሞች ቁርአን ተፎካካሪ ሊፈጠርለት እንደማይችል ከልክከ በላይ በራስ በመተማመን እንናገራለን ለቁርአን ግድድር መልስ የሚሰጥ ለ ፉርቃ ለሰ ሀፇ በሚል ርዕስ የተጻፈውን መጽሐፍ ሳገኝ ያደረብኝን መደመም ማሰብ ትችላላችሁ እውነተኛ መለኪያ ተብሎ የተተረጎመው ይህ መጽሐፍ በቁርአናዊ አጻጻፍ የከርስትናን ትምህርት የሚያቀርብ ነውጮ ይህ መጽሐፍ የቁርአንን አጻጻፍ ተከትሎ የተጻፈ ከመሆኑ የተነሳ አንዳንዶች በአደባባይ ሲያነቡት ቁርአንን አራሱን በማንበባቸው ምክንያት አረብ ሙስሊሞች አንኳ ሲያመሰግኗቸው ተሰምቷል ቁርአን ስለ ራሱ ያቀረበው ሙግት ማንም እርሱን የሚመስል መጽሐፍ መፍጠር አለመቻሉን ነው ነገር ግን ይህንን ተግዳሮት የሚመልስ መጽሐፍ ተገኝቷል ይህ ዜና ለኔ አስደንጋጭ ነበር ፉርቃ ፇ የሚለው መጽሐፍ አደገኛ መሆኑን ለመናገር እኔ ብቸኛ ሰው አይደለሁም ቢያንስ አንዲት አገር ያንን አድርጋለች ለደህንነታችን ስንል ይህንን መጽሐፍ ወደ አገር ውስጥ ማስገባት የተከለከለ ነው ይህ ደግሞ የትኛውንም የመጽሐፉን ከፍል ዳግም ህትመት ወይም ትርጉም እንዲሁም በውስጡ የሚገኘውን የትኛውንም ከፍል ያካተተ የትኛውንም ጽሑፍ ያጠቃልላል በኔ አመለካከት ማንም ይህንን የቁርአን ተግዳሮት መመለስ አይችልም ነበር ይህንን ካየሁ በኋላ ግን ይህ ተግዳሮት እኔ ካሰብኩት የተለየ ትርጉም እንዳለሁ ደመደምኩኝ አስቸጋሪውን ሁኔታ በማለፍ ሌሎች ሙግቶችን ማሰባሰብ ጀመርኩኝ ሙስሊም ዓቃቤ እምነታውያን ቁርአን ስለ ራሱ መለኮታዊነት ባቀረበው መከላከያ ብቻ አይወሰኑም በተደጋጋሚ እንደ ማስረጃ የሚጠቅሷቸው አራቱ ሙግቶች የሚከተሉት ናቸው የተፈፀሙ ትንቢቶች የሒሳብ ቁጥር ድግግሞሾች ሳይንሳዊ አውነታዎችና የጽሑፉ አለመለወጥ እያንዳንዱን በየተራ ለመፈተሽ ተነሳሁኝ ዓላማዬ ተዓማኒነታቸውን መፈተሽ ሳይሆን ለአስልምና አዎንታዊ የሆነ ማስረጃ በማቅረብ የእስልምና እውነትነት እኔን ጨምሮ ለኡማ በሙሉ ግልፅ የሆነውን ያህል ለጠያቂም ግልፅ አንዲሆን ማድረግ ነበር የመጀመርያዎቹ ሁለቱ ሙግቶች ፈጥነው ወደቁ በቁርአን ውስጥ አሳማኝ ትንቢት የለም አንዳንድ ትንቢት የሚመስሉ ጥቅሶች ቢኖሩም ቁርአን ግን እንደ ትንቢት አያቀርባቸውም ዝርዝር ጉዳዮችን ስለማያቀርቡ ጠንካራና ተጨባጭ የሆነ ሙግት ሊፈጥሩልኝ አይችሉም በተመሳሳይ በቁርአን ውስጥ የሚገኙት የሒሳብ ስሌቶች መለኮታዊ መሆኑን ያሳያሉ የሚል እምነት የለኝም አብዛኞቹ መረጃዎች ትርጉማቸው የተዛባና ከልከ በላይ የተለጠጡ ናቸው ሌሎቹ ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዲሁም በኤድጋር አለን ፖ ልበወለድ ውስጥና አልፎ ተርፎም በድረ ገፆች ላይ ልናገኛቸው የምንችላቸው ዓይነት ናቸው አስደሳቹ ነገር አነዚህ ሁለቱ ሙግቶች የኔ ንፅረተ ዓለም መሠረታዊ ሙግቶች አንደሆኑ በመማር አለማደጌ ነው የተቀሩት ሁለቱ ሙግቶች መሠረታውያን ናቸው ያለ መለኮታዊ መገለጥ መሐመድ ሊያውቃቸው የማይችላቸው ዘመን ተሻጋሪ ሳይንሳዊ አውነታዎች በቁርአን ውስጥ መኖራቸውን ከልጅነቴ ጀምሮ ስማር ነበር እነዚህ ሳይንሳዊ እውነታዎች የቁርአን ደራሲ ራሱ አላህ መሆኑን ያረጋግጣሉ ከሳይንሳዊ ሙግቱም በላይ ሙስሊሞች ቁርአን ሳይለዋወጥ ተጠብቆ መቆየቱን በፅኑ ያምናሉ ሙስሊሞች አንድ ነቁጥ እንኳን እንዳልተለወጠ ያምናሉሱ አላህ ሱራ ላይ ቁርአንን እንደሚጠብቅ ቃል ገብቷል ተጠብቆ መቆየቱ አላህ ለቃል ኪዳኑ ታማኝ መሆኑን እንደሚያሳይ ሙስሊሞች ያምናሉ የሳይንስ ሙግት በተለይም ደግሞ ቁርአን ያለምንም እንከን ተጠብቆ መቆየቱ የእምነቴ የማዕዘን ድንጋይ ነው የእምነቴ መሠረት ለሆነው የእስልምና ሙግት ጠንካራ ማረጋገጫ የሚሆኑ ፍሬዎችን ማፍራት እንደሚችሉ ተስፋ በማድረግ እነዚህን የማዕዘን ድንጋዮች ለመፈተሽ በአጭር ታጥቄ ተነሳሁኝ ነዚህ የማዕዘን ድንጋዮች ውድቅ ከሆኑ ምን ይፈጠር ይሆን። በሚል የመረረ ከርከር ተደርጎ ነበር በወቅቱ መሐመድ እዚያው ስለነበር ሁለታቸሁም በትክክለኛው መንገድ እያነበነባቸሁ ነው በማለት አረጋግቷቸዋል ከእናንተ በፊት የነበሩት ሕዝቦች የጠፉት በልዩነቶቻቸው ምከንያት ነው በማለት እርስ በርቸው እንዳይለያዩ ምከር ለግሷቸዋል መሐመድ ከሞተ በኋላ ብዙ ሰዎች ሙስሊሞች ሆነው የመኖር ፍላጎት አልነበራቸውም አቡበከር ሙስሊሞች ከሓዲያኑን በመዋጋት እስላማዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ሰደዳቸው ሙስሊሞቾ የቀድሞ ሙስሊሞችን ሲዋጉ ሳሉ ቁርአንን በቃላቸው ያጠኑትን ጨምሮ ብዙዎቹ በጦርነቱ አለቁ ጦርነቱ የሚቀጥል ከሆነ አቡበከር አብዛኛው የቁርአን ከፍል አንዳይጠፋ ስለሰጋ ዘይድ ኢብን ጣቢት በተሰኘ ሰው የበላይ ተቆጣጣሪነት ቁርአን በአንድ ጥራዝ እንዲሰበሰብ አዘዘ ሳሂህ አልቡኻሪ ሙስሊሞች የቁርአን አንቀፆችን በቀላሉ እንደሚረሱ በአፅንዖት ይናገራል ከዚህ የተነሳ ቁርአንን የመሰብሰብ ኃላፊነቱ ዘይድን በአጅጉ አድከሞት ነበር አንቀፆቹን ከግለሰቦች ትውስታና ከተለያዩ ቁርጥራጭ መጻፍያዎች ለይ ነበር የሰበሰበው ከአንድ በላይ በሆኑ አጋጣሚዎች የተወሰኑ የቁርአን አንቀፆችን ማስታወስ የቻለው አንድ ሰው ብቻ ነበር ዘይድ ሥራውን ካጠናቀቀ በኋላ የቁርአን ጥራስ ከመሐመድ መበለቶች መካከል በአንዷ ቤት እንዲቀመጥ ተደርጎ ነበር የማሰባሰብ ተግባሩ ዋነኛ ዓላማ አንድም የቁርአን ጥቅስ አንዳይጠፋ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ዘይድ በስህተት የዘለላቸው የቁርአን ጥቅሶች መኖራቸው ተደርሶበታል ከዚህም አልፎ በተለያዩ የሙስሊም ግዛቶች ውስጥ የሚኖሩት ብዙ ሙስሊሞች ቁርአንን በተለያዩ መንገዶች ያነበንቡ ስለነበር ይህ ሕዝብ በቁርአን ላይ ካለው ልዩነት የተነሳ ከመጥፋቱ በፊት የትድግና ተግባር እንዲከናወን ሙስሊም መሪዎች ጠይቀው ነበር በልዩነቶች ላይ አንዳያተኩሩ የሚገልፀውን የመሐመድን ምክር ችላ በማለት ኸሊፋ ዑስማን ቁርአን አንድ ወጥ መልከ እንዲኖረው ትዕዛዝ ሰጠ በመሐመድ መበለት ዘንድ የነበረውን ቅጂ በመውሰድ የዕርማት ሥራ ከሰሩለት በኋላ በመገልበጥ ወደ እያንዳንዱ የሙስሊም ግዛት አሰራጩት ከዚያም በቁርአን ላይ የነበረውን ከረከር ለማብረድ ዑስማን በቁርጥራጮች ላይ የተጻፉትም ሆኑ ሙሉ ቁርአኖች አንዲቃጠሉ አዘዘ ይህ እንግዲህ በሳሂህ አልቡኻሪ ውስጥ የሚገኘው የቁርአን አሰባሰብ ታሪከ ነው ሙስሊሞች አንዳቸው ለሌላቸው ከሚነግሩት በተፃራሪ ሳሂህ አልቡኻሪ ያቀረበው ታሪከ አንደ መሐመድ ታሪከ ሁሉ የበለጠ ወደ እውነት የተጠጋ ግርድፍ ታሪከ ነው እኔ በተማርኩት ታሪከ መሠረት መሐመድ ቁርአንን ለጸሐፊያን ይነግራቸዋል እነርሱም ይጽፋሉ ሙስሊሞችም ደግሞ ይሸመድዱታል መሐመድ ሲሞት ብዙ ሰዎች ቁርአንን በጽሑፍና በሽምደዳ ይዘው ነበር ዘይድ ኢብን ጣቢት ቁርአንን ኦፊሴላዊ በሆነ ሁኔታ ለመጻፍ የመጀመርያው ሰው ሲሆን በቃሱ ሸምድዶት ስለነበር ብዙም አልከበደወም ነበር የአርሱ ቁርአን በቃላቸው በሸመደዱት ሌሎች ዋና ዋና ሙስሊሞች ማረጋገጫ የተሰጠው ነው እኔ የተማርኩት ይህንን ነበር በስፋት ተቀባይነት ባገኘው መረጃ መሠረት በይዘቱ ላይ ምንም ከርከር አልነበረም ደካማ ትውስታ የሚባል ነገር አልነበረም ይጠፈሉ ተብለው የተሰጉ ምንባቦች አልነበሩም ነጠላ ምስከሮች አልነበሩም የተረሱ ጥቅሶች አልነበሩም በእርግጠኝነት ደግሞ ልዩነቶችን በማስወገድ ለመደበቅ የተደረገ አዋጅ አልነበረም በሳሂህ ቡኻሪ ውስጥ የተዘገበው የቁርአን አሰባሰብ ታሪከ የቁርአን ጥቅሶች እንዲጠፉ ሰፊ የሆነ በር የሚከፍት ጥንቃቄ የጎደለው ሥራ ነው በእርግጥ ሳሂህ ቡኻሪ ይህንን በግልፅ አስቀምጧል ዘይድ ቁርአንን አንድ ወጥ መልክ ባስያዘ ጊዜ ኡበይ ቢን ካእብ የተሰኘ ሰው ያነበንባቸው የነበረውን የተወሰኑ ከፍሎች አስወግዶ ነበር ኡበይ ዘይድ ያዘጋጀውን ቁርአን ችላ በማለት እነዚህን ጥቅሶች ማነብነብ እንደማይተውና የዚህ ምከንያቱ ደግሞ ከመሐመድ ስለሰማቸው መሆኑን ተናግሮ ነበር በሳሂህ ቡኻሪ ኑዛዜ እጅግ ደነገጥኩኝ ለምንድነው አስተማሪዎቹ ሁሉንም ታሪከ ያልነገሩኝ። አለው እርሱም እንዲህ አላቸው በጠበበው በር ለመግባት ተጋደሉ እላችኋለሁና ብዙዎች ሊገቡ ይፈልጋሉ አይችሉምም ባለቤቱ ተነሥቶ በሩን ከቄለፈ በኋላ እናንተ በውጭ ቆማቸሁ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ ክፈትልን አያላችሁ በሩን ልታንኳኩ ትጀምራላችሁ እርሱም መልሶ ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም ይላችኋል አብርሃምንና ይስሐቅን ያዕቆብንም ነቢያትንም ሁሉ በእግዚአብሔር መንግሥት ባያችሁ ጊዜ አናንተ ግን ወደ ውጭ ተጥላችሁ ስትቀሩ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል ከምሥራቅና ከምዕራብም ከሰሜንና ከደቡብም ይመጣሉ በእግዚአብሔርም መንግሥት በማዕድ ይቀመጣሉ ማንበብ አቁሜ መጽሐፉን አስቀመጥኩት መደመም ይዞኛል አግዚአብሔር ትርጉም የማያስፈልገውን ግልፅ ህልም አሳይቶኛል ይህ ትርጉም ለሁለት ሺህ ዓመታት ያህል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሰፍሯልጠባቡ በር ወደ ደህንነት የሚያስገባ በር ነው ወደ እርሱ ለመግባት የተቻለኝን ሁሉ አንዳደርግ ኢየሱስ እየነገረኝ ነው በመንግሥተ ሰማያት ማዕድ ተቀምጩ መካፈል እንድችል ለዳዊት ግብዣ ምላሽ መስጠት አንዳለብኝ ከህልሙ ተረድቻለሁ ምላሽ ካልሰጠሁ በውጪ ቆሜ ወደ ውስጥ ለመግባት ብለምን መግባት አይቻለኝም በደህንነት ጠባብ በር ላይ ቆሜ ወደ ውስጥ ለመግባት ለምን እንዳልተፈቀደልኝ ግራ ገብቶኛል ደስ የሚለው ነገር የቤቱ ጌታ በመምጣት በሩን አልዘጋብኝም አሁን ያልተመለሰልኝ ጥያቄ የለም ምን ማድረግ እንዳለብኝ አውቄያለሁ ግብዣውን መቀበል ይኖርብኛል ምዕራፍ ሃምሳ ከመስጊድ የሚያስወጣው ቀጥተኛ መንገድ ሦስት ህልሞችን የጠየኩ ሲሆን እግዚአብሔር ከመታመን የሚያልፈውን ቸርነቱን አሳየኝ ኤፕሪል ረፋድ ላይ ሦስተኛውን ህልም አገኘሁኝ ነጫጭ ደረጃዎች ባሉት መስጊድ ውስጥ በመጀመርያው ደረጃ ላይ ተቀምጫለሁ ደረጃዎቹ ማስጌጫዎች ያሏቸው ሲሆን ወደ ግራ አቅጣጫ የተጠመዘዙ የአጅ መያዣዎች አሏቸው ደረጃዎቹ የተሠሩበትን ቁስ አላስታውስም ነገር ግን ከእብነ በረድ ወይም ከአንጨት የተሰሩ እንደሆኑ እገምታለሁ የደረጃው ጫፍ ላይ ፊቴን አዙሬ ተቀምጫለሁ በዚህ ህልም ውስጥ ሆፔ ከአኔ በስተቀኝ ካለው አቅጣጫ ራሴውኑ መልሼ አመለከት ነበር በደረጃው ላይ ተቀምጩ ከእንጨት ወደተሰራው ቡናማ ምስባከ እየተመለከትኩኝ የሆነ ሰው ንግግር አንዲያደርግ አየተጠባበኩ ያለሁ ይመስለኛል ከፍሉ አረንጓዴ ምንጣፍ ያለው ሲሆን ሰዎች እዚያ ላይ እንዲቀመጡ ይጠበቅባቸዋል እኔ ግን ደረጃው ላይ መቀመጤ ምንም ችግር እንደሌለው ይሰማኝ ነበር አኔ ከተቀመጥኩበት ደረጃ በስተግራ ባለው ከፍት ቦታ ሰዎች መጥተው እንዲቀመጡ አጠባበቅ ነበር በከፍሉ በስተቀኝ በኩል ምንም እንቅስቃሴ አልነበረም ከፍሉ ቀስ በቀስ እየሞላ ሲመጣ ኢማሙ በስተግረዬ በኩል ወደ ኋላ ትንሽ ፈንጠር ብሎ ወለሉ ላይ ተቀምጧል ነጭ ልብስ ለብሶ አንደ ሴሎቹ ሰዎቸ ሁሉ እርሱም ተናጋሪውን ይጠባበቅ ነበር እኔ ስጠባበቅ የነበረው እርሱን ሲሆን ቅዱስ ሰው ሆኖ እንደማንኛውም ሰው ከእኔ ኋላ በወለል ላይ መቀመጡ አስገርሞኛል ደግሞም ግራ ገብቶኛል አከብሮቴን ለማሳየት ከደረጃው ላይ ወርጄ ከእርሱ በስተ ጀርባ ወለሉ ላይ ልቀመጥ ብፈልግም ነገር ግን ካለሁበት መነሳት አልቻልኩኝም በሆነ በማይታይ መግነጢሳዊ ኃይል ከተቀመጥኩበት ቦታ ጋር የተሰፋሁ መስሎ ይሰማኝ ነበር ይህ ኃይል ምቾት በመንሳት ጨምቆ የሚይዝ ዓይነት ባይሆንም ነገር ግን እንደ ፈለኩ እንድሆን የሚፈቀድ ዓይነት አልነበረም ወለሉ ላይ አጣብቆ ይዞኛል ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም ነበር ከፍሉ ውስጥ የነበሩት ሰዎች ምን እንደሚጠባበቁ አላውቅም ነበር ተናጋሪው ማን ሊሆን እንደሚችል ምንም የማውቀው ነገር አልነበረኝም በአንደህ ዓይነት ግራ መጋባት ውስጥ ሆፔ ህልሙ ተጠናቀቀ ለእኔ ህልሙ ግልፅ መልዕከት ያለው ነው ከመስጊድ በሚያስወጣው ደረጃ ላይ ተቀምጫለሁ ከዚህ ቀደም የማከብራቸው ሙስሊሞች ከእኔ በታችና ከእኔ ኋላ ተቀምጠዋል አከብሮት ላሳያቸው ብሞከርም ከእነርሱ ኋላ ባለው የቀድሞ ቦታዬ ላይ ሄጄ መቀመጥ ተስኖኛል ከኋላዬ የተውኳቸው ሲሆን ከመስጊድ በሚያስወጣው መንቋ ላይ ነኝ ይህ እንዲሆን ውሳኔው የእግዚአብሔር ነው ከዚህም በላይ ደግሞ የምንጠባበቀው ሰው ኢማሙ አይደለም ምናልባት ከእርሱ የላቀ ሥልጣን ያለውን ሰው እየተጠባበቅን ሊሆን ይችላል ይህ ሰው ደግሞ ምናልባት ጭራሹኑ ወደ መስጊዱ ላይመጣ ይችላል ይህኛውም ህልም እንደ ሁለተኛው ህልም ሁሉ ያለሁበትን ቦታ አንጂ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አልነገረኝም የሚመጣውን እየተጠባበኩ ነበር ነገር ግን አርሱ ሊመጣበት በሚችለው ትክክለኛ ቦታ ላይ ባለመሆኔ ግራ ተጋብቻለሁ በዚህ ህልም ውስጥ መስጊድና ኢማም ስለሚገኙ እማ እንድትተረጉምልኝ ነገርኳት የኢብን ሲሪንን መጽሐፍ በመጠቀም ትተረጉምልኝ ጀመር ደረጃዎቹ በዚህም ሆነ በመጪው ዓለም ደረጃዬ ከፍ ማለቱን አንደሚያመለከት በመጀመርያው ደረጃ ላይ መቀመጤ ጉዞዬን ገና መጀመሬን አንደሚያመለከት በህልሙ መጀመርያ ላይ መስጊዱ ባዶ መሆኑ የሃይማኖት ትምህርት ልማር እንደሆነ እንደሚያመለከት ወደ መጨረሻ አካባቢ መስጊዱ መሙላቱ አስተዋይ የሆነ የሃይማኖት መምህርና ውጤታማ አማካሪ እንደምሆን አንደሚያመለከት ኢማሙ ሙስሊውን ኡማ በሙሉ አንደሚወከልና ነጭ ልብስ መልበሱ ልባቸው ቀና መሆኑን አንደሚያመለክከት ነገረችኝ ከእኔ ኋላና ከአኔ በታች የመቀመጡን ሚስጥር ልትፈታ አልቻለችም በምንጣፍ ላይ የመቀመጡንም ትርጉም ልትነግረኝ አልቻለችም አንድ ሰው በምንጣፍ ላይ ተቀመጦ ማየት ያ ሰው መሳሳቱንና ሀሰተኛ የሆኑ መረጃዎችን ሊሰጥ እንደሚትል ያሳያል የህልሙ ትከከለኛ ትርጉም እንደተሰወረባት ብትደመድምም ነገር ግን ጥሩ ዜና ያዘለ መሆኑን ተረድታች ህልሙን ለዳዊት ስነግረው የሰጠኝ ምላሽ ይበልጥ ትርጉም የሚሰጥ ነበር ከመስጊድ የሚያስወጣ ደረጃ ነቢል ምን ነካህ። ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ ሆፔ ከአግዚአብሔር ጋር ሙግት ገጠምኩኝ ቤተሰቦቼ የመከዳት ስሜት እንዳያድርባቸው ባመንኩበት በዚያው ቅፅበት ብትገድለኝ ይሻለኝ ነበር ከሞቴ ይልቅ ይህ ለእነርሱ እጅግ የከፋ ነው ቢያንስ ፍቅራችን ይቀጥል ነበር ቢያንስ ቤተሰባችን አንድ ሆኖ ይኖር ነበር እግዚአብሔር ሆይ ለምን የሕይወቴ ከባድ የሰቆቃ ጊዜ በነበረው በዚያው ሰዓት ከእኔ ሥነመለኮትና አስተሳሰብ የወጣ አንድ ነገር ተከሰተ እግዚአብሔር ሜጋፎን አንስቶ በህሊናዬ ውስጥ የተናገረ ይመስል እንዲህ የሚል ድምፅ በመላው እኔነቴ ውስጥ ሲሰራጭ ሰማሁ ምከንያቱም ይህ ስለ አንተ ጉዳይ ባለመሆኑ ነው አፌን ከፍቼ ቀረሁ እንባው መነፋረቁ መንቀጥቀጡ በሙሉ በአንድ ጊዜ ቀጥ አለ በኤሌክትሪክ ንዝረት እንደተመታና ራሱን እንደሳተ ሰው ሆፔ መሬቱ ላይ ተዘርሬ ቀረሁ ለአሥር ደቂቃዎች ያህል መንቀሳቀስም ሆኔ አፌን መከደን ተስኖኝ ቆየሁ ውስጤን እያደሰው ነበር መንቀሳቀስ ስቸል ኀዘኔ በሙሉ ጠፋ በሰቆቃ ውስጥ ሆፔ የተናገርኳቸው የጸሎት ቃላት ባለፈው ሕይወቴ ውስጥ የተነገሩ ዓይነት ሆነዋል ከመሬት ተነስቼ ዙርያ ገባውን ማየት ጀመርኩኝ ዛፎቹን ሰማዩን የቆምኩባቸውን ደረጃዎች አጤንኳቸው ነገር ግን ዓለምን በተለየ መንገድ ማየት ጀምሬያለሁ ከዚህ ቀደም ባለቀለም መነፅሮችን ነበር ሳደርግ የነበረው አሁን ግን ሁሉም ወልቀዋል ሁሉም ነገር የተለየ ሆኖ ታየኝ አንድ በአንድ የመመርመር ፍላጎት አደረብኝ ከዚህ ቀደም ደግሜ ደጋግሜ ያየሁትን አንድ ነገር አስተዋልኩኝ ወደ ኅከምና ትምህርት ቤት እየሄደ ያለ ሰው ነገር ግን ያየሁት እርሱን ብቻ አልነበረም ይህ ሰው ማን እንደሆነ ባላውቅም ነገር ግን ከራስ ጋር በሚደረግ ትግል የተሞላ ሕይወት እንዳለው የተበላሸ የፍቅር ግንኙነት አንዳስጨነቀውና ለራስ ዝቅተኛ የሆነ አመለካከት በመስጠት የታሰረ ሕይወት እንዳለው ተረዳሁ ዕውር በሆነ ዝግመተ ለውጥ የመጣ መሆኑን በማመኑ ምክንያት ሳያውቀው ለራሱ የሰጠው ግምት ዝቅተኛ ሆኗል የተራ ፅድል ውጤት እንደሆነ ያምናል ደስታን አሳዳጅ በመሆን የበለጠ የጥፋተኝነት ስሜት እንዲያድርበት ካደረገው የሕይወተ ዘይቤ የዘለለ ዓላማ ተስፋና ትርጉም የለውም አነዚህን ደስታዎች ማሳደድ የጥፈተኝነት ስሜት እንዲያድርበትና ታማሚ እንዲሆን አድርጎታል ይህንን ችግሩን ለማሸነፍ የሚያሳድደው ሌላ አዲስ ደስታ ለበለጠ የህሊና ቁስልና ህመም ዳርጎታል እነዚህን ችግሮች ችላ በማለትና አዙሪቱን የሚሰብርበትን መንገድ ባለማወቅ ቀኑን ለመኖር ከቤቱ ወጥቷሰ የተመለከትኩት ሰው እግዚአብሔር ነፃ ሊያወጣው እንደሚቸል ማወቅ የነበረበትን ሰው ነው ይህ ሰው ስለ እግዚአብሔርና ስለ ኃይሉ ችሎት ማወቅ ይኖርበታል ያውቅ ይሆን። ሪረያ የነ ኩባሚ ውድ ወዳጆቼ የኔን ታሪከ ስላነበባቸሁ በጣም አመሰግናለሁ ጌታ በዚህ ታሪከ ተጠቅሞ ስለ እስልምና ፅውቀት እንድትጨብጡ እአንዲረዳችሁና ኢየሱስን አንዲሁም ፍቅሩን የበለጠ በመረዳት እንዲባርካቸሁ ጸሎቴ ነው የሕይወት ታሪኬን ሳካፍል ሰዎች በተደጋጋሚ የሚጠይቋቸው ጥያቄዎች አሉ የመጨረሻውን መልዕከቴን ከማስተላለፌ በፊት የናንተም ጥያቄዎች አንደሆኑ የምገምታቸውን ጥቂቶቹን አመልሳለሁ ኢየሱስን ከተቀበልኩ ከጥቂት ቀናት በኋላ ዳዊት የፒ ኤች ዲ ትምህርቱን ለመከታተል ወደ ኒው ዮርክ ተንቀሳቀሰ አንዳለመታደል ሆኖ ቤተ ከርስቲያኒቱን አንደ መጋቢ ያገለግል የነበረው አርሱ በመሆኑ አካባቢውን ለቆ ሲሄድ አባላቱ ተበተኑ እኔም ብቻዬን ቀረሁ በዚህ ጊዜ የነበረኝ ብቸኛ ከርስቲያን ጓደኛ ቢኖር ከአኔ ጥቂት ወራት በመቅደም የጌታ ኢየሱስ ተከታይ የሆነው ዛከ ነበር ሁለታችን ከሌሎች ሁለት አዳዲስ አማኞች ጋር በመሆን በየሳምንቱ ረቡዕ አንሰበሰብ ነበር ለአንድ ሰዓት ያህል ረዕዶጎ መምታጓጋየሚለውን የቻርለስ ዝዊንዶልን መጽሐፍ ካነበብን በኋላ ቀሪዎቹን ጥቂት ሰዓታት መጽሐፍ ቅዱስን በማንበብ እናሳልፍ ነበር አንዳንድ ጊዜ ለእግዚአብሔርና ለቃሉ ካለን ጥማት የተነሳ ሌሎች ሥራዎቻችንን በመርሳት እስከ ሌሊቱ አሥር ሰዓት መጽሐፍ ቅዱስን እናጠና ነበር በጋራ እንጸልይ ነበር እንፆም ነበር ጥቅሶችን አንሸመድድ ነበር አንዲሁም የጌታን ፊት በፅኑ እንፈልግ ነበር በነዚህ ጊዜያት ተዓምራትን አይተናል ትንቢቶችንና ራዕዮችን ተቀብለናል አጋንንት እንኳ ሲወጡ ተመልክተናል ከከርስቶስ ጋር በነበረኝ ጉዞ ጅማሬ አካባቢ የኖርኩት ወርቃማ ጊዜ ከሰባት ወራት በኋላ አከተመ መጽሐፍ ቅዱስን ከጨረስኩኝ በኋላ የበለጠ ጊዜ ለትምህርት በመስጠት የቃሉን ጥናት ቀነስኩኝ ቤተ ከርስቲያንን ስለተቀላቀልን የረቡዕ ምሽት መርሃ ግብራችን እየቀነሰ መጣ በዙርያዬ በነበረው የየዕለት ኑሮ ተመልሼ ስለተጠመድኩኝ ልዕለ ተፈጥሯዊ ተዓምራቱ ተገቱ ዳዊት ለከረምት አረፍት ተመልሶ ሲመጣ አገልግሎት አብረን ጀመርን እኔና ዳዊት ሜይ ላይ በወቅቱ አዲስ ርዕስ ለነበረው የዳን ብራውን ሟሯ ይድ መጽሐፍ መልስ የሚሆን ትምህርት በኖርፎልከ ቨርጂንያ ሴንትራል ባፕቲስት ቤተ ከርስቲያን እሁድ አምልኮ ላይ አስተማርን በአገልግሎቱ መጨረሻ ላይ ሁለት አምላክ የለሾች ወደ ፊት በመምጣት ከርስቶስን ተቀበሉ ለአገልግሎት መጠራታችንም ተረጋገጠ ሚኒስትሪያችንን ናኔፖሥፈፅዕ ዓቃን ዎታዶ በማለት የሰየምነው ሲሆን የመልዕከታችን ማዕከል የሆነውን የከርስቶስን ትንሣኤ የሚያመለከት የግሪከ ቃል ነው አናስታሲስ ዓቀበተ አምነት የሚለው ስም ለመጥራት ትንሽ የሚያስቸግር አንደሆነ ስለተሰማን ዖፅ የሐዋርያት ሥራ ወደሚል ቀየርነው ቤተሰቤን በተመለከተ ደግሞ ከድንጋጤው ካገገሙ በኋላ እኔን በተመለከተ ሁለት ነገሮችን ግልፅ አደረጉ አንደተከዱ ቢሰማቸውም ነገር ግን ፍቅራቸው አልቀነሰም ነበር ቁጣ ቢነድም መጥፎ ቃላት ቢነገሩም ከርከር ቢጦፍም ነገር ግን ከቤተሰብ አባልነት አልሰረዙኝም ነበር በአንድ ወገን ይህ ትልቅ በረከት ነው ምክንያቱም የቤተሰቤ አባል ሆፔቼ ቀጥያለሁና በሌላ ወገን ደግሞ በየጊዜው የስሜት ማዕበላትን ማስተናገድ ስለነበረብኝ በጣም ከባድ ነበር እማ የቤተሰቡን ደስታ በማደፍረሴ ምክንያት ለተከታታይ ሁለት ዓመታት በምሬት ታለቅስ ነበር በነዚያ ጊዜያት ፊልጵስየስ ሉቃስ እና ማቴዎስ የመሳሰሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ከፍሎች በማንበብ እፅናና ነበር ከውድ ባለቤቴ ጋር የተዋወቅሁት በ ሲሆን ከአንድ ዓመት በኋላ ጥያቄ አቅርቤላት ከአራት ወራት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ጋብቻ ፈፀምን ከአምስት ተወዳጅ የአጎቴ ልጆችና ከአንድ አጎቴ በስተቀር ከቤተሰቤ የእኔ ሰርግ ላይ የተገኘ ማንም አልነበረም እንደርሱ መሆኑ በእጅጉ ያሳዘነኝ ሲሆን አሁንም ድረስ ሳስበው ህመም ይሰማኛል በ ከኅከምና ትምህርት ቤት ስመረቅ የኅከምና ሥራ ከመሥራት ይልቅ ሙሉ ጊዜዬን ለአገልግሎት ለመስጠት ወሰንኩኝ ቤተሰቦቼ ይህንን ውሳኔዬን ሲሰሙ ከእኔ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ሁሉ አቋረጡ ከዓመት በኋላ መነጋገር የጀመርን ሲሆን ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ግንኙነታችን በየመሃሉ ይረባበቫል ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ከተከሰቱት ያልታሰቡ ነገሮች የተነሳ ከጁን ጀምሮ አከትስ ዓቀበተ እምነት በንግግር ነፃነት ሸሪኣ በምዕራብ አገራትና እስልምና ላይ ማተኮር ጀመረ ወንጌልን በማሰራጨት ብቻ ላይ ያተኮረ ምኒስትሪ መጀመር እንዳለብኝ ስለተሰማኝ ከአክትስ በመለየት ሰሬድ የተሰኘ ምኒስትሪ ጀመርኩኝ ከራቪ ዘካርያስ ጋር በ መጨረሻ ላይ ተዋውቄ ጁላይ ላይ ምኒስትሪውን ተቀላቀልኩኝ በመጨረሻም ከርስቶስን ለመከተል ሊወስኑ ላሉቱ በተለይም ደግሞ ይህንን በመወሰናቸው ብዙ መስዋዕትነት አንደሚከፍሉ ለሚያውቁቱ መልዕከቴን ለማስተላለፍ እፈልጋለሁ አውነቱን ለመናገር እንደ ከርስቲያን ያሳለፍኩት የመጀመርያው ዓመት ከሚታሰበው በላይ አስቸጋሪ ነበር በሕይወቴ ውስጥ እጅግ የተሰቃየሁበት ጊዜ ነበር እያንዳንዷ ቀን በትግል የምታልፍ ሲሆን ከዚያ ቀደም ያላየሁትን ጥልቅ የስሜት መረበሽ አስተናግጃለሁነገር ግን ደግሞ ከስምንት ዓመታት በኋላ ዞር ብዬ ሳየው የሕይወቴ ጠንካራ ጊዜ እንደነበር ልናገር አቸላለሁ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ወደመሆን በመቅረፅና በማስተካከል ለውጦኛል መንፈስ ቅዱስ አፅናፔ ነበር ቃሉ ደጋፊዬ ነበር ያንን ጊዜ በምንም ነገር ልለውጠው አልችልም አውነተኛ የኢየሱስ ተከታይ ያደረገኝ ያሳለፍኩት መከራ ነበር ከጌታ ጋር ያለኝን ጉዞና ከውዷ ባለቤቴ ጋር ያለኝን ትስስር ጨምሮ አሁን ያለኝ ሕይወት ሙስሊም ሆኘፔ አስብ ከነበረው በላይ እጅግ ግሩም ነው በየትኛውም መከራ ውስጥ ብናልፍ አንኳን ኢየሱስን መከተል አዋጭ የሆነ ምርጫ ነው እርሱ እጅግ ድንቅ ነው ውድ ወዳጆቼ አንድ ቀን ተገናኝተን ስለ ደስታችንና ስላሳለፍነው መከራ እግዚአብሔርን በጋራ ማመስገን እንችል ዘንድ ጸሎቴ ነው በከርስቶስ የናንተው ነቢል ቁሬሺ ሣስታዉጠሻቻች ይህ ምልከት በአረብኛ ሥ ዳፅጀ ወፅጎምየሚለውን የሚወከል ሲሆን የአላህ ሰላምና በረከት በአርሱ ላይ ይሁን ማለት ነው ሙስሊሞች የመሐመድን ስም ከጠቀሱ በኋላ የሚናገሩት ነው ታዝ ወዖዓ የሚለው ይህ አነጋገር የአላህ ስም ከተጠራ በኋላ የሚደጋገም ነው ትርጉሙም የተከበረና ከፍ ያለ ማለት ነው በአላህ እጠጋለሁ የሚል ትርጉም ያለው የተለመደ የሙስሊሞች ንግር ሲሆን አንድ ጥሩ ያልሆነ የከህደት ወይም አሉታዊ የሆነ ቃ ሲነገር የሚባል ነው በእስልምና አላህ ስሞች እንዳሉት ይታመናል ሁለቱ ይቅር ባይ እና አዛኝ የሚሉ ናቸው ከብር ለአላህ ይሁን የሚል እጅግ የተለመደ የሙስሊሞች ንግር ሲሆን መልካም ዜና ወይም ደስ የሚያሰኝ ነገር ሲነገር ብዙ ጊዜ በአንከሮ ይነገራል ሙስሊሞችን የሚያመለከት ማሕበረሰብ የሚል ትርጉም ያለው የአረብኛ ቃል ነው ከከ ከ መለኮታዊ መገለጥ በእርሱ ላይ መጣ የነቢዩ ፊት ቀላ ቁና ቁና ይተነፍሱ ነበር ከዚያም እፎይታ ተሰማቸው በተጨማሪም ከከ እበ የአላህ ነቢይ መገለጥ ሲመጣላቸው በቀዝቃዛ ቀን አንኳ ያልባቸው ነበርሹ የተለመደ የንስሐ ንግግር ሲሆን ከአላህ ምህረትን አሻለሁ ማለት ነው ከከ እበ ሙስሊም ዓቃቤ እምነታውያን ዘዳግም መሐመድ ወደ መካ በድል ስለገባበት ሁኔታ የተተነበየ ትንቢት እንደሆነ ይናገራሉ የቁርአን ንባብ ብቸኛ አማራጭ የሆነ ከ ላከህ ሀበ ከከ ህከቨ ይህ ዘገባ ከብዙ ንግግሮች የተሰበሰበ ሲሆን አንዳንዶቹ በተደጋጋሚ የሰማኋቸው ሌሎቹ ደግሞ የተሳተፍኩባቸው ናቸው ይህ ምናልባት የቀደመው እስልምና በስልጣናዊ አገዛዝ የሚያምን ከመሆኑ ጋር የተያያዘ ሊሆን ይቸላል ወይም ደግሞ በዚህ ዘመን ያሉት ሙስሊሞች በአንፃራዊነት ፊደል የመቁጠራቸው የመጀመርያው ታላቁ ጦርነት በመባል በእስላማዊ ታሪኮች ውስጥ የሚታወቀው የበድር ጦርነት ሁኔታ አናሳ በመሆኑ ምከንያት በአፍ ከአንዱ ወደ ሌላው የሚሸጋገር ታሪክ አስፈላጊ በመሆኑ ምከንያት ሊሆን ይቸላል ሮሜ ገላቲያ እብፇል ከሀበ ላ ከቧ ፀኗሀ ከ በ ሀሃ ከ ከ ከሃ ከከ ኪ ይህ የተሻሻለ ህትመት ነው አሕመዲ ጀማት ሱራ መንፈሳዊ አርገትን እንጂ ሥጋዊ እርገትን አንደማያመለከት ያስተምራሉ ይህ በርግጥ ማርቆስ አና ሉቃስ በተሳሳተ መንገድ ማቅረብ ሲሆን በሙስሊሞች ሙግት ውስጥ በብዛት ይስተዋላል በሁለቱም ቦታዎች ላይ ኢየሱስ ቸር መሆኑን አላስተባበለም ከከ ሀእከቨ ሱኒዎች አንዳንዴ በሙዋታ ኢማም ማሊከ የመጨረሻዎቹ ሦስቱ ላይ አይግባቡም እንኳ መሐመድ በመካ የሲራራ ነጋዴዎች ላይ በፈፀሙት ጥቃት ምከንያት የተደረገ ነበር የመኸላ ዘመቻ በመባል ይታወቃል ከከ ፌከበ ለ ህ ከ ዐ ሀወሪር ዐወዐዘዐዘ ዐ ህዘ ዐ ወናዘ ለሀጸከ እፀ ኘ ዐር ርዐኗያብ ዐከሁ ይመልከቱ ከከ እከ የአላህ መልዕከተኛ እንዲህ ብለዋል ሰዎች ከአላህ በስተቀር ሊመለከ የሚገባው እንደሌለና መሐመድ የእርሱ መልዕከተኛ መሆኑን አስኪመሰከሩ ድረስ ሓ እንዲሁም ሰላትን ደንቡን ጠብቀው እስኪሰግዱ ድረስ እንድዋጋቸው ታዝዣለሁ ይህንን ካደረጉ በአስልምና በተወሰነው ምከንያት ካልሆነ በስተቀር ነፍሳቸውንና ንብረታቸውን ከእኔ ይታደጋሉ ድርሻቸውም በአላህ ይታሰብላቸዋል ከከ እሀበ ኡመር እንዳስተላለፈው የአላህ መልዕከተኛ አንዲህ ብለዋል አይሁድና ክርስቲያኖችን ከአረብያ ባሕረ ሰላጤ አስወጣቸዋለሁ ከሙስሊም በስተቀር አንዱንም አልተውም ፐከፀ ጳከፀኗ ዐ ከአፀ ዐዐከፀኒ ከር ርንሀቧኪ ከሰ በአል ቡኻሪ ውስጥ በጂሃድ ርዕስ ስር የሰፈረውን ማንበብ ብቻ ይህንን ግልፅ ያደርጋል ከ የቀደሙትንም ሆነ የአሁኖቹን እስላማዊ ጽሑፎች ስናነብ መንፈሳዊ ጂሃድን የተመለከቱ መረጃዎች በጣም ጥቂት ሆነው እናገኛቸዋለን ዛሬ ምዕራባዊ ባልሆኑ ቋንቋዎች አረብኛ ፋርስ ኡርዱ በመሳሰሉት የሚጽፉ ሙስሊሞች ጂሃድ በዋናነት ነውጠኛ አለመሆኑን ወይም መንፈሳዊ ትግል መሆኑን በፍፁም አይገልፁም እንዲህ ያሉ ብሂሎች በብቸኝነት በምዕራባውያን ምሑራን በሱፊዎች በሃይማኖት ውይይቶች ላይ በሚሳተፉ ወይም እስልምናን በተቻለ መጠን ተቀባይነት ባለው መንገድ ለማቅረብ በሚሞከሩ ዓቃቤ እምነታውያን የሚነገሩ ናቸው።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF


Download options | Convert to Pdf | Advertise on dirzon

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact